Friday, 28 June 2013 19:27

አድማስ አድቨርታይዚንግ

Written by 
Rate this item
(15 votes)


አድማስ አድቨርታይዚንግ እ.ኤ.አ በ1990 የተቋቋመ የግል ድርጅት ነው፡፡ አድማስ አድቨርታይዚንግ ሃላፊነቱ የተወሰነ የግል ኩባንያ ሁለት ዋና ክፍሎች አሉት፡፡

የህትመቱ ክንፍ አንዱ ሲሆን ሳምንታዊው ጋዜጣ አዲስ አድማስ ያሳትማል የማስታወቂያ ክንፉ ደግሞ የፊልም መስሪያስቱዲዮ እና ግራፊክ ዲዛይን ያለው ነው፡፡ ድርጅታችን በኤሌክትሮኒክስ ሆነ በህትመት ሚዲያ ላይ የሚሰራ የማስታወቂያ ኤጀንሲ ነው፡፡ የቴሌቪዢንና ሬዲዮ ማስታወቂያዎችን በመስራት በአየር ላይ ከማዋላችንም በተጨማሪ የሚዲያ ምክርና ዕቅድ አገልግሎቶች እንሰጣለን፡፡ በሚሰጠን ቅድመ መረጃ አማካይነት ማናቸውንም የቲቪ፣ሬዲዮ እና ፕሬስ ማስታወቂያዎች እንዲሁም ግራፊክ አርትስ እንሰራለን፡፡

አገልግሎታችን በሚዲያ ምርጫ ላይ ማማከር፣ማቀድ፣መከታተል፣የማስታወቂያዎቹ ያስገኙትን የመጨረሻ ውጤት መገምገምን ያካትታል፡፡ በርፉ ያልን በቂ ልምድና በቡድን የመስራት ባህል ሚዲያውን እንዴት ደንበኞቻችን በሚያረካና ውጤታማ በሚያደርግ መልኩ መጠቀም እንዳለብን እንድናውቅ አስችሎናል፡፡ አድማስ አድቨርታይዚንግ የአዲስ አበባ ንግድ ም/ቤት አባል ሲሆን በተለያዩ ባህላዊና ማሕበራዊ እንቅስቃሴዎች ንቁ ተሳታፊ ነው፡፡

Audio visual studio

የማስታወቂያ አገልግሎት እና ኦዲዮ/ቪዥዋል ስቱዲዮበላቀ የፕሮዳክሽን ደረጃው ዪታወቀው የማስታወቂያ ክፍላችን ለንግዱ ዘርፍና ለማህበራዊ ግብይት ዋነኛ አጋርነቱን አረጋግጧል፡፡ ፕሮፌሽናል የኦዲዮ/ቪዲዮ ስቲዲዮችን፡፡ በፕሮፌሽናል ዲቪ ካሜራዎች ከአማራጭ ሌልሶች ጋር የመብራትና የድምጽ መሳሪያዎች የካሜራ ክሬን በተሟላ የኤዲቲንግ ስቱዲዮ እና በሌሎች ተፈላጊ መሳሪያዎች የተደራጀ ነው፡፡ ቴክኖሎጂ ያፈራቸውን የተደራጀ ዘመናዊ መሳሪያዎች የያዘው ስቱዲዮአችን በአገራችን ካ ጥቂት ምርጥ የፊልም ስቱዲዮዎች አንዱ ያደርገዋል፡፡

አድማስ አድቨርታይዚንግ ብቁና ተፎካካሪ በሆኑ የአስተዳደር የፋይናንስ እና በጥበብ ባለሙያዎች የተሞላ ነው በድርጅቱ የሚሰሩት ተርጓሚዎች ገጣሚዎች የአርት ዳይሬክተሮች እና ጋዜጠኞች በሙያቸው የተሞከሩ የተፈተኑና በበርካታ ፕሮጀክቶች አመርቂ ውጤት ያስመዘገቡ ናቸው፡፡ በተጨማሪው ድርጅቱ በህዝቡ ዘንድ በተቀዳጀው አክብሮት እና አስተማማኝ የሥራ ሁኔታ የተነሳ በአገሪቱ የሚገኙ ምርጥ የፈጠራ ችሎታ ያላቸው ባለሙያዎች ለመቅጠርና አብረውን እንዲሰሩ ለማድረግ አስችሎታል፡፡ ለዚህም በየጊዜው ያስመዘግባቸው የስኬት ክብረወሰኖች ከቃላት በላይ ይናገራሉ፡፡

የአድማስ አድቨርታይዚንግ ኃ/የተወሰነ የግል ማህበር ሥራ አስኪያጅ የነበሩት አቶ አሰፋ በኢትዮጵያ የማስታወቂያ ኢንዱስትሪ ጉልህ ለውጥ ማምጣታቸውም ይታወቃል፡፡

በኢትዮጵያ በተፈጠረው የዲሞክራሲ ስርዓት ሚዛናዊ ሂሳዊ ጋዜጣ በመመስረት ለህብረተሰቡ የንባብና የዕውቀት ዕድል የፈጠረ ሰው ነበር፣ያሉት በቀብር ሥርዓቱ ላይ የተገኙት የማስታወቂያ ሚኒስትሩ አቶ በረከት ስምኦን ሲሆኑ የሪፖርተር ጋዜጣ ባለቤትና ዋና አዘጋጅ አቶ አማረ አረጋዊ በበኩላቸው ‹‹ በኢትዮጵያ ፕሬስ የተግባር ሚና ከተጫወቱ ሰዎች ግንባር ቀደም ነው ›› ብለዋል፡፡የአቶ ድንገተኛ ሞት አስመልክተው ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ አስተያየታቸውን ሲሰጡዕ ‹‹ እንደ ህብረተሰብ ትልቅ ሰው ነው ያጣነው ›› ብለዋል፡፡

በብዙዎች ዘንድ አድንቶትን ያተረፈውንና በስምንት ድምፃውያን የተዜመውን ‹‹ ማውቀር ነው መሰልጠን ›› የተሰኘ የዘፈን ክሊፕ ከተለያዩ ድርጅቶች ጋር በመቀናጀት አድማስ አድቨርታይዚነግ ማሰራቱ የማታወቅ ሲሆን በቅርቡ በኮራ አሸናፊ የሆነው የድምፃዊት ፀደንያ ገ/ማርቆስ የዘፈን ክሊፕ አቶ አሰፋ እራሳአው በቅርቡ ባቋቋሙት የፊልም ስቱዲዮ መሰራቱ ታውቋል፡፡

በአድማስ አድቨርታይዚንግ ስር የሚታተመውና በአገራችን በስርጭት ብዛት ከሁለት ዓመት ወዲህ በቀዳሚነት ሥፍራ የሚገኘው የአዲስ አድማስ ጋዜጣ መስራች ስራ አስኪያጅ የሆኑት አቶ አሰፋ ከምዕራብ አገራት የፊልም ደረጃ ጋር የሚስተካከል ፊልም ለመስራት ባላቸው ራዕይ ለየት ያለ ስቲዲዮ በመገንባት ላይ ነበሩ፡፡


Read 7256 times