Saturday, 29 June 2013 10:51

“የሺ ሀረጊቱ” በመፅሐፍ መጣ “ኢትዮጵያን ማን ይታደጋት” ገበያ ላይ ዋለ

Written by 
Rate this item
(3 votes)

በአንጋፋው ድምፃዊ መሐሙድ አህመድ በ“የሺ ሀረጊቱ” የተሰኘ ዘፈን መነሻነት የተፃፈው ልቦለድ መፅሐፍ ታትሞ ለንባብ ቀረበ፡፡ በዚህ ሳምንት እየተሰራጨ ያለውን መፅሐፍ የደረሰው ደጀኔ ተሰማ ነው፡፡ 235 ገፆች ያለውን መፅሐፍ ያተመው እታፍዘር ማተሚያ ቤት ሲሆን አከፋፋዩ ሊትማን ጀነራል ትሬዲንግ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ነው፡፡ መፅሐፉ በ40 ብር ለገበያ ቀርቧል፡፡ በሌላም በኩል በጋዜጠኛ አቤል አለማየሁ እና ኤልያስ ገብሩ የተዘጋጀው “ኢትዮጵያን ማን ይታደጋት” መፅሐፍ ለንባብ በቃ፡፡

ጋዜጠኞቹ 255 ገፆች ባለው መፅሐፋቸው ከ12 ምሁራን፣ ጋዜጠኞች፣ የሐይማኖት ልሂቃን እና ፖለቲከኞች ጋር የተደረጉ ሙግቶችና ውይይቶች አካተዋል፡፡ በመፅሐፉ ያለፈው መንግሥት ከፍተኛ ባለስልጣን የነበሩትና ዘንድሮ ህይወታቸው ያለፈው ኮሎኔል ደበላ ዲንሳ የመጨረሻ ቃል፣ የሃይማኖት መቻቻል፣ ሕገመንግስት፣ የብርቱካን ሚደቅሳ ፖለቲካ የሚሉና ሌሎች ርእሰ ጉዳዮች ተካተዋል፡፡ መፅሐፉ በሀገር ውስጥ በ49.60 ብር በውጭ ሀገራት በ20 ዶላር ለገበያ ቀርቧል፡፡

Read 3662 times