Saturday, 13 July 2013 12:05

50 ሴንት አምስት ዓመት በሚያሳስር ጥፋት ተከሰሰ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

ታዋቂው ራፐር 50 ሴንት በቀድሞ ፍቅረኛው ላይ አድርሷል በተባለ ጥቃት ሊከሰስ ነው፡፡ ጥፋተኛ ሆኖ ከተገኘ የአምስት አመት እስርና የ46ሺ ዶላር ካሳ እንዲከፍል እንደሚወሰንበት የቢልቦርድ ዘገባ አመልክቷል፡፡ 50 ሴንት ከሁለት ሳምንት በፊት ወደ ቀድሞ ፍቅረኛው የኮንዶሚኒዬም መኖርያ በመሄድ ጥቃት ማድረሱ ተገልጿል፡፡ በሌላ በኩል ከፈፀመው ፆታዊ ጥቃት ጋር በትችት መወጠሩ ሳያንሰው ራፐሩ በስልክና በፅሁፍ መልዕክት የ16 ዓመት ልጁን በማስፈራራቱም እየተብጠለጠለ ነው፡፡ ራፐሩ ከታዳጊ ልጁ ጋር በስልክ ባደረገው ንግግር “የእናትህ ልጅ እንጂ የእኔ አይደለህም፡፡ ገና የደም ምርመራ ሁሉ አደርጋለሁ፡፡ እንደ እናትህ እና እንደ ቤተሰብህ ከእኔ የምትፈልገው ስጦታ ብቻ ነው፡፡ ከእንግዲህ ግን ምንም እንዳትጠብቅ፡፡ ስልኬን ሰርዘው፡፡ ሁለተኛም እንዳትደውልልኝ” ብሎታል፡፡

ቢልቦርድ መፅሄት እንደዘገበው፤ ራፐሩ በቀድሞ ፍቅረኛው እና በልጁ ላይ የፈፀማቸው ተግባራት ገፅታውን እያበላሸበት ነው፡፡ በሌላ በኩል ፊፍቲ ሴንት ከሙዚቃው ባሻገር በተሰማራበት ንግድ እጅግ ትርፋማ እየሆነ መምጣቱን ያመለከተው ሂፖፕ ኒውስ፤ በ260 ሚሊዮን ዶላር ከአምስቱ የዓለም ሃብታም ራፐሮች አንዱ ሊሆን እንደበቃ ጠቁሟል፡፡ ለ50 ሴንት ሃብት ማደግ በዋናነት “ቪታሚን ዎተር” በተባለው የውሃ ምርት አምራች ኩባንያ ያዋለው ኢንቨስትመንት ትርፋማነት መሆኑን የጠቀሰው ዘገባው፤ ‹ጂ ዩኒት› በተባለው የፋሽንና የሙዚቃ ኩባንያው እንዲሁም በፊልም ስቱድዮው እና በተለያዩ የማስታወቂያ ስራዎችም የተወጣለት ነጋዴ መሆኑን አብራርቷል፡፡

Read 2012 times