Saturday, 13 July 2013 12:11

ፈንዲቃ የባህል ቡድን በሞንታና ፎልክ ፌስቲቫል ይሳተፋል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

ትናንት በተከፈተው የሞንታና ፎልክ ፌስቲቫል ፈንዲቃ የባህል ቡድን ኢትዮጵያን በመወከል እንደሚሳተፍ ተገለፀ፡፡ ከ200 አገራት የተውጣጡ የሙዚቃ ቡድኖችና የፋሽን ባለሙያዎች የሚሳተፉበት ዓለም አቀፉ የሙዚቃ ፌስቲቫል እስከ 31 ሚሊዮን ዶላር የሚደርስ የንግድ ስራዎች የሚንቀሳቀስበትና ከ16ሺ በላይ ጎብኝዎች የሚገኙበት ነው፡፡ ፈንዲቃ የኢትዮጵያ አዝማሪ ባንድ እና የባህል ውዝዋዜ ቡድን ሲሆን ስድስት ሙዚቀኞች፤ ሁለት ተወዛወዦች እና አንድ ድምፃዊን በማቀፍ በሞንታና ፎልክ የሙዚቃ ፌስቲቫል በመሳተፍ የአገር ባህልን በማስተዋወቅ ከፍተኛ ትኩረት ያገኛል ተብሏል፡፡ ፈንዲቃ የባህል ቡድን ከአምስት ዓመት በፊት በተወዛዋዥነቱና በባህል አምባሳደርነቱ በሚታወቀው አርቲስት መላኩ በላይ እንደተመሰረተ ይታወቃል፡፡

Read 1766 times