Error
  • JUser: :_load: Unable to load user with ID: 62
Saturday, 19 November 2011 14:41

የአድቬንቸር ፊልሞች ገበያ ደርቷል

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

ባለፈው ሳምንት በሰሜን አሜሪካና በሌሎች 35 የዓለም ሲኒማዎች የታየውና በግሪክ አፈታሪክ ላይ የተሰራው አድቬንቸር ፊልም “ዘኢሞርታልስ” በ70.3 ሚሊዮን ዶላር ሳየቦክስ ኦፊስን የገቢ ደረጃ የሚመራ ሆኖል፡፡ በ75 ሚሊዮን ዶላር በጀት የተሰራው “ዘኢሞርታልስ” በዓለም ዙርያ በገቢ ስኬታማ መሆኑ በአድቬንቸር የሆሊውድ ፊልም ሰሪዎች ያተኮሩበትን ሁኔታ አጉልቶታል፡፡ በላዮን ጌትስ ኩባንያ የሚሰራጨው ዘኢሞርታልስ በተመሳይ ጭብጥ ለእይታ ከበቁ ሌሎች ፊልሞች ያገኙትን ገቢ ግን አላሳካም፡፡ በመጀመርያ ሳምንታቸው በመላው ዓለም ሲታዩ ከ250 ሚሊዮን ዶላር በላይ ያስገቡት “300” እና “ዘ ክላሽ ኦፍ ታይታንስ” የተባሉት የግሪክ አፈታሪክ ፊልሞች ናቸው፡፡

ከሆሊውድ ፊልም ሰሪ ኩባንያዎች በዘንድሮው የዓለም ገበያ 19.2 በመቶ ድርሻ በመያዝ በአድቬንቸር ፊልሞቹ ስኬታማ የሆነው ፓርማውንት ፒክቸርስ እንደሚመራ ያመለከተው ቦክስ ኦፊስ ሞጆ በ2011 የወጡ ፊልሞች አጠቃላይ ገቢ 8.57 ቢሊዮን መድረሱን አመልክቷል፡፡ ዋርነር ብሮስ 17.8 ፤ቡዌና ቪስታ 13.2 ፤ሶኒና ኮሎምቢያ 12.7 እንዲሁም ዩኒቨርሳል ፒክቸርስ 11.5 በመቶ የገበያ ድርሻ ኖሯቸው እስከ 5 ያለውን ተከታታይ ደረጃ አግኝተዋል፡፡ ዘንድሮ 19 ፊልሞችን በዓለም ዙርያ ለእይታ ያበቃው ፕርማውንት ፒክቸርስ ገቢው 1.56 ቢሊዮን ዶላር ተመዝግቧል፡፡በሆሊውድ ፊልም ሰሪ ኩባንያዎች በዓመቱ የተሰሩ ፊልሞች 1.05 ሚሊዮን ትኬቶች በ7.97 ዶላር አማካይ ዋጋ እንደተሸጠላቸው ያሳየው የቦክስኦፊስ ሞጆ መረጃ ከዓመቱ ጠቅላላ ገቢ 34 የአድቬንቸር ፊልሞች 2.05 ቢሊዮን ዶላር ገቢ በማስመዝገብ ከፍተኛውን ድርሻ መያዛቸውን ጠቅሷል፡፡

 

Read 2919 times Last modified on Saturday, 19 November 2011 14:43