የአዲስ አድማስ ፎቶ ጋዜጠኛ የሆነው አንተነህ አክሊሉ ያነሳቸው ከ30 በላይ ፎቶግራፎች የተካተቱበት “ላይት ኢን ሻዶው” የፎቶግራፍ አውደርእይ ካዛንቺስ በሚገኘው ኦዳ ታወር የፊታችን ሐሙስ ከምሽቱ 12 ሰዓት እንደሚከፈት አዘጋጁ አስታወቀ በኦዳታወር ሶስተኛ ፎቅ በቅርቡ በተከፈተው ኮክ ቺክን ባር እና ሬስቶራንት የሚከፈተው አውደርእይ “ጥበብ፣ ከተማና ገጠር” በሚል መሪ ቃል የሚካሄድ ሲሆን ባለፉት ሰባት ዓመታት ፎቶግራፈሩ በሀገሪቱ የተለያዩ ክፍሎች ተዘዋውሮ ያነሳቸው ምርጥ ፎቶግራፎች ይካተቱበታል፡፡ የፎቶግራፍ ኤግዚብሽኑ እስከ ነሐሴ 20 ለሕዝብ ክፍት ሆኖ ይቆያል፡፡