የአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ እና በባህርዳር የሚገኘው የሙላለም የባህል ማዕከል ሚሊኒየሙ የባህል ቡድን በጋራ ያዘጋጁት ህገወጥ የሰዎች ዝውውርን የሚያወግዝ ኪነጥበባዊ ፕሮግራም እየቀረበ ነው፡፡
የዛሬ ሳምንት በባህርዳር መቅረብ የጀመረው ዝግጅት፤ ግጥሞች፣ሙዚቃ፣ የ25 ደቂቃ ድራማ እንዲሁም ውይይት ተካሂዶበታል፡፡ ተመሳሳይ ዝግጅቶችን የችግሩ ሰለባ በሆኑ ዞኖች እንቀጥላለን ያሉት የባህል ማዕከሉ የፕሮሞሽን ቡድን አስተባባሪ አቶ ሰለሞን ታደሰ ከሌቻ፤ ተዘዋዋሪ የኪነጥበብ ዝግጅቱ ለውጥ ያመጣል ተብሎ ተስፋ እንደተጣለበት ተናግረዋል፡፡ ዝግጅቱ ከሚቀርብባቸው ከተሞች መካከል ወልዲያ፣ወረኢሉ፣መተማ እና ከሚሴ ይገኙበታል፡፡
Saturday, 17 August 2013 12:34
በአማራ ክልል ህገወጥ የሰዎች ዝውውር ላይ ያተኮረ ኪነጥበብ እየቀረበ ነው
Written by Administrator
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና