Saturday, 24 August 2013 11:10

“እንግዳ ነፍስ” ፊልም ሰኞ ይመረቃል “ጃንኖ” ፊልም በአዲስ አበባ መታየት ጀመረ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

በአሊ ይመር ተጽፎ የተዘጋጀውን “እንግዳ ነፍስ” ፊቸር ፊልም ሰኞ ምሽት በኢትዮጵያ ብሔራዊ ትያትር እንደሚያስመርቅ ዙምባራ ፊልም ፕሮዳክሽን አስታወቀ፡፡ በፊልሙ ላይ መንትዮችን ጨምሮ 45 ያህል ተዋንያን እንደተሳተፉበት የጠቀሰው ድርጅቱ፣ፊልሙን ሠርቶ ለማጠናቀቅ አንድ ዓመት እንደፈጀ አስታውቋል፡፡
በሌላም በኩል “ጃንኖ” የተሰኘ ፊልም የ95 ደቂቃ ፊልም በአዲስ አበባ መታየት ጀመረ፡፡
በሐዋሳ ተሰርቶ በዚየው ከተማ ሰኔ 26 ተመርቆ የነበረው ፊልም ባለፈው እሁድ በአለም፣ በዋፋ፣ በዮፍታሔ፣ በሴባስቶፖል፣ በኢዮሃ፣ በሆሊሲቲ ሲኒማ ቤቶች ታይቷል፡፡
ፊልሙን ፋሲል አስማማው ጽፎ ፕሮዲዩስ ያደረገው ሲሆን በደረጄ ደመቀ ዳይሬክተርነት ዘነቡ ገሠሠ፣ እንቁሥላሴ ወ/አገኘሁ፣ አልጋነሽ ታሪኩ፣ ናርዶስ አዳነ፣ ተመስገን ታንቱ፣ ይልፋሸዋ መንግስቴ ደረጄ ደመቀና ሌሎችም ተውነውበታል፡፡

Read 1477 times