Saturday, 24 August 2013 11:26

ደራሲዋ በመፅሃፍ ሽያጭ 95ሚ. ዶላር አፈሰች

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

ኢ.ኤል ጄምስ ትባላለች፡፡ ፎርብስ መጽሔት ባወጣው የደራሲዎች አመታዊ ሽያጭ ዝርዝር አንደኛ ሆናለች - “50 ሼድስ ኦፍ ግሬይ” በተሰኘ መፅሃፏ፡፡ ከዚ መፅሃፍዋ ያገኘችው የገንዘብ መጠን 95 ሚሊዮን ዶላር ነው፡፡ መጽሐፉ በሦስት ተከታታይ ክፍል (Trilogy) የሚተረክ ሲሆን በስምንት ወር ውስጥ ሰባ ሚሊዮን ኮፒ ተሸጧል፡፡ መጽሐፏን ወደ ፊልም ለመቀየር በሲኒማ ሰሪዎች ተጠይቃ በመስማማቷ ተጨማሪ አምስት ሚሊዮን ብር ትርፏ ላይ ታክሎላታል፡፡ በ2014 ፊልሙ ሲኒማ ቤቶችን ያናውጣል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
ከዚህች ሴት ደራሲ (ኢ.ኤል ጄምስ) ድንገተኛ ስኬት በፊት ከፍተኛ ሻጭ የነበረው ጄምስ ፓተርሰን ነበር፡፡ ዘንድሮ ሁለተኛ ደረጃን ይዟል፡፡ ሴቷ ደራሲ በአራት ሚሊዮን ብር በልጣ አስከትላዋለች፡፡ ለአራት ተከታታይ አመታት የያዘውን ደረጃም ነጥቃዋለች፡፡ ጄምስ ፓተርሰንን “አሌክስ ክሮስ” እና “ማክሲመም ራይድ” በተሰኙ ድርሰቶቹ ድፍን አለም ያውቀዋል፡፡ በአመት አምስት መጽሐፍት ጽፎ (አምርቶ) ለማሳተም በመብቃቱ ይጠቀሳል፡፡ እሱን በመከተል ሶስተኛ ደረጃ ላይ ያለችው ሱዛን ኮሊንስ ናት፡፡ 55 ሚሊዮን ዶላር ትርፍ ከመጽሐፏ ሽያጭ አግኝታለች፡፡ መጽሐፏ “ዘ ሀንገር ጌምስ” ይሰኛል፡፡ ወደ ፊልምም ተቀይሯል፡፡ በዚሁ አመት የ”ሀንገር ጌምስ” ተከታይ የሆነው ፊልም “ዘ ሀንገር ጌምስ ካቺንግ ፋየር” የሲኒማን አለም እንደሚነቀንቅ ይጠበቃል፡፡

Read 1814 times