Monday, 18 November 2013 11:42

ግማሽ-መንገድ መሄድ ይቅር- “የዲጄ”አይደለም ድምፃችን

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

ግማሽ-መንገድ መሄድ ይቅር እንዝለቅ እስከጐሉ ጫፍ
ድጋፍ የለም በግማሽ-አፍ’ ከልባችን እንደግፍ!
የወረት ነው የሚመስል-ካሸናፊ ጋራ እፍ-እፍ
አኪሩ ሲዞር ማቀርቀር-ተሸናፊን ረግጦ ማለፍ!
መቼ በኳስ ብቻ ሆነ - ታይቷል በሌላም ምዕራፍ፡፡
ቋሚ እንሁን እንጽና’እንጂ ከእሳት ወደ በረዶ
መወንጨፍ ከጽንፍ ወደ ጽንፍ
ክñ አመል ነው ዥዋዥዌ-ዛሬ ጓዳ@ነገ ደጃፍ”
ስናገባ ብቻ ዘራፍ!
ስንሸነፍ ጉልበት ማቀፍ!
ሲሞቅ እንደ እንፋሎት መትነን@
ሲበርድ እንደግዑዝ ነገር’ፍፁም ዲዳ በድን መሆን
እሪ ስንል ጐል አግብተን’ያመት-ባል ገበያ መስለን@
በለስ ነስቶን ድል ባይቀናን
ሬሳ የወጣው ቤት መሆን@
ኧረ ጐበዝ! ቋሚ እንሁን !
ገብቶ መፋለም ቢያቅተን
መደገፍ እንዴት ይጥፋብን?!
ከፊልሙ እንዳልተዋደደ
ከግብሩ እንዳልተዋሃደ
ከትወናው ጋራ ሠምሮ’ወጥ ሆኖ አብሮ እንዳልሄደ
ከቦክስ ኋላ እንደሚመጣ’የቀሽም ፊልም አጃቢ ድምጽ
ከድርሰቱ እንደተፋታ’እንዳላማረ ኮሾ አንቀጽ
ሙሉ ጨዋታ መደገፍ’መጮሁ እንዴት ያቅተን?
በቴፕ አፍ የተፈጠረ’የዲጄ ነው እንዴ ድምፃችን?
ባገርም ጉዳይ ይሄው ነው፡-
ቅጥ-አንጣ በድላችን
ሲበልጡን ቆፈን አይያዘን-
መቼም መቼም የትም ቢሆን
ሙሉ ጊዜ ቋሚ እንሁን! እናግዝ ልጆቻችንን!
መቼም ኢትዮጵያዊነትን’የውጪ ባዕድ አልሰጠን
እኛው ውስጥ የበቀለ እንጂ’ “የዲጄ” አይደለም ድምፃችን
ብንሸነፍም እኛው’ብናሸንፍም እኛው ነን!
በወረት አንለዋወጥ’እንደግፍ ከልባችን!
እናግዝ አገራችንን!!
(ለኢትዮ-ናይጄሪያ የኳስ ፍልሚያና ለኢትዮጵያውያን ደጋፊዎች) ኀዳር 2 ቀን 2006 ዓ.ም

Read 2926 times