Monday, 18 November 2013 11:58

“...በአንድ ማዕከል...ሁሉን አገልግሎት...”

Written by  ፀሐይ ተፈረደኝ (ከኢሶግ)
Rate this item
(0 votes)

እ.ኤ.አ ኦክቶቨር 17/20013 በኢትዮጵያ ደግሞ ጥቅምት 7/2006 ዓ/ም ጾታን መሰረት ባደረገ ጥቃት ምክንያት ለሚደርሱ የአካል፣ የስነልቡና ፣የህግና የጤና ችግሮች በአገር አቀፍ ደረጃ በአንድ ማእከል ተመሳሳይ አገልግሎት ለመስጠት እንዲቻል አንድ ወጥ መመሪያ በማስ ፈለጉ በተዘጋጀው ረቂቅ ላይ ውይይት ተደርጎአል፡፡ በኢፊድሪ ጤና ጥበቃ ሚኒስ..ር አስተባ ባሪነት ከህግ፣ ከፖሊስ ከስነልቡና ፣ ከሴቶች ወጣቶች እና ህጻናት ሚኒስ..ር የተውጣጡ ሙያ ተኞች በኢትዮጵያ የጽንስና ማህጸን ሐኪሞች ማህበር ፕሮጀክት ቢሮ ስብሰባውን ሲያደርጉ የማህበሩ አባላት እና የፕሮጀክቱ አስተባባሪዎች አስፈላጊውን ገለጻ አድርገዋል፡፡ ይህንን ረቂቅ በማዘጋጀት ረገድም በኢትዮጵያ ጽንስና ማህጸን ሐኪሞች ማህበር ፕሮጀክቱን ሲመሩ የቆዩ የማህበር አባላት ከፍተኛ አስተዋጽኦ አድርገዋል። ስብሰባውን እንዲከፍቱ የተጋበዙት የጽንስና ማህጸን ሐኪሞች ማህበር ፕሬዝዳንት ዶ/ር ይርጉ ገ/ሕይወት ነበሩ፡፡ ዶ/ር ይርጉ እንደገለጹት...
“...የስብሰባው አላማ የጾታዊ ጥቃት የደረሰበት ሰው ወደ ሕክምና በሚመጣበት ጊዜ ሊደረግለት የሚገባው አገልግሎት በምን መልክ መሆን አለበት የሚለውን ለመፈተሸ ነው፡፡ የጾታዊ ጥቃትን በሚመለከት ለሚሰጠው ስልጠና ካሪኩለም ተዘጋጅቶ በአገር አቀፍ ደረጃ ስራ ላይ ውሎአል፡፡ ነገር ግን የስራ ሂደቱን በሚመለከት ወጥነት የሚጎድለው አካሄድ ስለአለ አሁን የሚደረገው ጥረት ይህንን ለማስተካከል ነው፡፡ በአብዛኛው ጾታዊ ጥቃት የሚደርስባቸው ሴቶች ስለሆኑ አንዲት ሴት ይህ ችግር ሲገጥማት ወደህክምና መስጫ ተቋም ወይንም ወደ ህግ ተቋም እንዲሁም ወደስነልቡና አገልግሎት ልትሄድ ትችላለች፡፡ ይህም አንዲት ጥቃት የደረሰባት ሴት በመጀመሪያ ልታገኛቸው የምትፈልጋቸው ተቋማት እንደሆኑ እርግጥ ነው። ነገር ግን መንገዱን ከጀመሩት በሁዋላ የሚገጥማቸው ችግር ቀላል የማይባል ነው፡፡ ...ለምሳሌ ወደ ጤና ተቋም ብትሄድ በመጀመሪያ ከፖሊስ ወረቀት አምጪ ልትባል ትችላለች። ወደህግ ቦታ ስትቀርብ ደግሞ ቅድሚያ ሊሰጣቸው የሚገቡ የህክምና ሁኔታዎች ቸል ሊባሉ የሚችሉበት አጋጣሚ ይኖራል። ስለዚህም የስራ ሂደቱ ወጥ ቢሆን እንዲሁም የሚሰሩት ስራዎች የህክምናው ለህግ ፣ የህጉ ለሕክምናው ግልጽ ቢሆኑ እንዲሁም የማህበራዊእና የስነልቡና ስራ የሚሰሩት ባለሙያ ዎች አሰራራቸው ግልጽ ቢሆን የሚሰጠው አገልግሎት የተሳካ ይሆናል፡፡ አገልግሎቱም በሁለት መልክ መፍትሔ የሚሰጥ ይሆናል የሚል እምነት ይኖራል፡፡
1. ጥቃትን መከላከል የሚያስችል ፣
2. ጥቃት ከደረሰም አስፈላጊውን እርዳት ሁሉ...ሕክምና...ሕግ...የማህበራዊና ስነልቡና አገልግሎት ድጋፍ መስጠት የሚቻልበት የስራ ሂደት ይፈጠራል .....ብለዋል፡፡
በረቂቅ ዶክመንቱ ላይ እንደሚነበበው...ጾታን መሰረት ያደረገ ጥቃት ሲባል ወንድንና ሴትን ሳይለይ በሁለቱም ላይ የሚደርሰውን ጥቃት የሚመለከት ቢሆንም በተለምዶ የሚታየው ግን በተለይ ሴቶች ከወንዶች ይልቅ በዚህ ዘርፍ ተጎጂ ሲሆኑ ነው፡፡ ለዚህም እንደ አንድ ምክንያት የሚጠቀሰው በወንዶችና ሴቶች መካከል ያለው ኃይል ወይንም አቅም ተመጣጣኝ አለመሆኑ ነው፡፡ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት አገላለጽ መሰረት በሴቶች ላይ የሚደርስ ጥቃት ጾታን መሰረት ያደረገ እና በአካል እንዲሁም ስነአእምሮ ላይ ጉዳት ከማድረሱም በተጨማሪ ተያይዞ ለሚመጣ የስነልቡና ጉዳት የሚዳርግ ነው፡፡
በሴቶች ላይ የሚደርስ ጥቃት አለምአቀፋዊ ሲሆን መሰረቱ እሩቅ የሆነ እንዲሁም ዘዴ የተሞላበት የኃይል አለመጣጣም የሚታይበት ከመሆኑም ባሻገር በሴቶችና በወንዶች መካከል ያለውን የአካል ተፈጥሮአዊ ልዩነት በግልጽ የሚታይበት ነው። በዚህም ምክንያት ጀንደር በሚለው የማህበራዊ ስርአት አወቃቀር ለሴቶች እና ለወንዶች ሲሰጥ የኖረውን ደረጃ እና የአኑዋኑዋር ዘይቤ ምን ያህል ሴቶች ላይ ጫና ያደርስ እንደነበር መገለጫው ነው፡፡ ለዚህ ምስክሩም ብዙውን ጊዜ ወንዶች በሴቶች ላይ የሚፈጽሙት ጥቃት በህብረተሰቡ ዘንድ እንደ ጥፋት ሳይቆጠሩ እንዲያውም የሚወሰደው የህግ እርምጃ አነጋጋሪ የሚሆንበት አጋጣሚ በብዙ ሀገሮች የሚስተዋል በመሆኑ ነው፡፡
በሴቶች ላይ የሚፈጸሙ ጥቃቶች የት እና እንዴት ወይንም በማን ተብሎ ሊከፋፈል የማይችል በአጠቃላይም የትም ቦታ ፣በማንኛውም ሰው ተብሎ ሊገለጽ እንደሚችል ጥናቶች ያስረዳሉ፡፡
በሴቶች ላይ የሚፈጸም ወሲባዊ ጥቃት በቤት ውስጥ፣ በመኖሪያ አካባቢ፣በትምህርት ቤት ፣በስራ ቦታ ...ወዘተ ሊደርስ እንደሚችል የተለያዩ ማስረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡
በሴቶች ላይ የሚደርሱ ወሲባዊ ጥቃቶች በቤተሰብ፣ በጉዋደኛ፣ በስራ ባልደረባ፣ በማያውቁት ሰው ...ወዘተ ሊፈጸሙ የሚችሉ ጉዳቶች ናቸው፡፡
በጾታ ጥቃት ምክንያት ጉዳት መድረስ ማለት የሰብአዊ መብትን እንደመጋፋት የሚቆጠር ነው፡፡ ለዚህም እማኝ የሚሆኑት የተለያዩ አለምአቀፋዊ መድረኮች ናቸው፡፡ ለምሳሌም...
(CEDAW) 1979, World conference on human rights ,Viena,1993, International conference on population and Development (ICPD),Cairo,1994, UN fourth conference of women ,Beijing ,1995,Declatation of the General Assembly of the united nations on the elimination of Violence against Women,,. Beijing platform of Action, Millennium Development goals(MDGs)…. ወዘተ
ከላይ ለምሳሌነት የተጠቀሱት አለምአቀፍ ስብሰባዎችና ሌሎችም መድረኮች በተስማሙበት መሰረትም በጾታ ጥቃት ያደረሰ ሰው አስፈላጊውን የህግ ቅጣት እንዲያገኝ ሐገሮች የተስማሙበት ሲሆን ለተጎጂዎችም የአካል ጤንነት እንዲሁም የህሊና ነጻነት የሚያስገኝ ነው፡፡
በወሲባዊ ጥቃት ምክንያት የሚደርሰው የጤና ችግር የህብረተሰብ የጤና ችግር ተደርጎ የሚወሰድበት መንገድም አለ። አንዲት ሴት በደረሰባት ወሲባዊ ጥቃት ምክንያት ከሚደር ሱት የጤና እውክታዎች መካከል ...የአካል ጉዳት...ከባድ የእራስ ሕመም...በቋሚነት ሊገጥም የሚችል የጀርባ ሕመም... የስነልቡና መቃወስ ...እንደ ድብርት ...ፍርሀት ...እንቅልፍ ማጣት ...መርሳት... በራስ የመተማመን ብቃትን ማጣት የመሳሰሉ ችግሮች ሊገጥሙዋት ይችላሉ፡፡ በዚህም ምክን ያት አብዛኛውን ጊዜ በእራሳቸው ላይ ጉዳት ለማድረስ የሚሞክሩ ሴቶች በርካታ ናቸው፡፡ የእና ቶችን ሞት ከሚያባብሱ መካከል የሚመደብ ሲሆን ለኤችአይቪ ኤድስ ተጋላጭ የሚሆኑትም ቀላል የሚባሉ ኤደሉም፡፡
ጾታን መሰረት ያደረገ ወሲባዊ ጥቃት የኢኮኖሚም ጉዳይ ነው፡፡ ለዚህ ተጋላጭ የሆኑ ግለሰቦች በሚደርስባቸው የጤና መጉዋደል ምክንያት የእራሳቸው እንዲሁም የቤተሰባቸው ገቢ ከመቃወሱ በተጨማሪ ለአገልግሎቱ የሚውለው ወጪ ብዙ ነው፡፡ አንድ ጥናት እንደሚያ መለክተው በባንግላዴሽ በ2010/ በአጠቃላይ የቤት ውስጥ ጥቃት በገንዘብ ሲሰላ 1.8/ቢሊዮን ዶላር ያህል ነበር፡፡ በ1996 እ.ኤ.አ በቺሌ በተደረገው ጥናት ሴቶች በሚደርስባቸው ወሲባዊ ጥቃት ምክንያት ሊያገኙት የሚገባቸውን ወደ 1.56/ ቢሊዮን ዶላር አጥተዋል፡፡ በዚሁ መልክ የተለያዩ ሐገሮችን እውነታ ጥናቶች የሚያሳዩ ቢሆንም ወደሀገራችን መለስ ስንል ግን ዝርዝር በሆነ መልክ መረጃውን ማግኘት የሚያስችል ጥናት አልተደረገም፡፡ ቢሆንም ግን ከተለያዩ መረጃዎች መረዳት እንደሚቻለው በገጠርም ይሁን በከተሞች ችግሩ በሰፋ መልኩ የሚስተዋል መሆኑን ነው። በወሲባዊ ጥቃት ብቻም ሳይሆን በአጠቃላይ በቤት ውስጥ ጥቃት ምን ያህል ሴቶች ተጎጂ ሆነዋል የሚለውን ለመለካት ባይቻልም እንኩዋን በ2011 /በአገር አቀፍ ደረጃ በተደረገው..ሃመ እንደተመለከተው ብዙ ሴቶች መብታቸውን እንደማያውቁና ወንዶችም ሴቶ ችን መጉዳት እንደጥፋት የማይቆጥሩት መሆኑን ነው፡፡ ለምሳሌም በዳሰሳ ጥናቱ ከተካተቱት ተሳታፊ ሴቶች 68 ኀ ወንዶች ቢመቷቸው ምንም ነውር እንደሌለበት የገለጹ ሲሆን 45 ኀ የሚሆኑት ወንዶች ደግሞ ሴቶች በወንድ መመታታቸው አግባብነት ያለው አድርገው እንደሚቀበሉት ተናግረዋል፡፡
በሴቶች ላይ የሚደርስ ጾታዊ ጥቃት ከልማት ጋር የሚያያዝ ጉዳይም ነው፡፡ የምእተ አመቱን የልማት ግብ ለማሳካት የሚያስችሉ ነጥቦችን መከወን በሴቶች ላይ የሚደርሰውን ጥቃት ለመቀነስ እንደሚረዳ እሙን ነው፡፡ አገራት በዚህ ዘርፍ በጥንካሬ መስራት እንደሚጠ በቅባቸው የአለም የጤና ድርጅት አስምሮበታል ..ሳሳቈስቋቋሽቃሸ ባሽቄቁስቃሰስ ሮሸሮሽቃቋ.. ብቄቂስቃ ሮቃሳ ሮሰሻሽስባሽቃሸ ..ሻስ ቂሽቁቁስቃቃሽበቂ ሳስባስቁቄቅቂስቃ.. ሀቄሮቁቋ ፡ሠሃሑ 2005...
የኢትዮጵያ የጽንስና ማህጸን ሐኪሞች ማህበር ፕሬዝዳንት ዶ/ር ይርጉ ገ/ሕይወት የጾታን ጥቃት በሚመለከት በማህበሩ ሲሰራ የቆየውን እና ወደፊት ምን ለማድረግ እንደሚገባ ሲገልጹ የሚከተለውን ብለዋል፡፡

.....ቀደም ባለው ጊዜ ይህንን ጥቃት በሚመለከት ደረጃውን ያልጠበቀ ሕክምና እና ደረጃውን ያልጠበቀ የህክምና ማስረጃ የሚሰጥበት ሁኔታ የነበረ ሲሆን እ.ኤ.አ ከ2001 -2002/ ድረስ ባለው ጊዜ የተወሰኑ ሞዴል ክሊኒኮችን በመስራት እና ወሲባዊ ጥቃት የደረሰባቸው ሴቶች በአንድ ተቋም ውስጥ የተሟላ አገልግሎት የሚያገኙበትን እና በተቻለ መጠንም በቂ የሆነ ሕጋዊ ማስረጃ የሚያገኙበትን ሁኔታ ሲያመቻች ቆይቶአል። ከዚያም በሁዋላ ይህንን በአዲስ አበባ ብቻ ሲሰጥ የቆየውን አገልግሎት ወደሌሎች መስተዳድሮችም በ ማስፋፋት በአዳማና በአዋሳ ሞዴል ክሊኒኮቹን በማመቻቸት ስራዎች እየተሰሩ ቆይተ ዋል፡፡ለወደፊቱም ያለው እቅድ አሁን ያሉትን ሞዴል ክሊኒኮች ከሁለት ወደሰባት ከፍ ለማድረግ ነው፡፡ ለዚህም ማእከላቱ የዩኒቨርሲቲ ሆስፒታሎች ናቸው፡፡ የዚህም ምክንያቱ በዩኒቨርሲቲ ሆስፒታሎች ጥራቱን የጠበቀ አገልግሎት መስጠት ከተቻለ ከዚያ የሚወጡ በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ የቅድመ ምረቃ እና የድህረ ምረቃ ተማሪዎች ወደስራ በሚሰማሩበት ወቅት አገልግሎቱን በተቻለ ፍጥነትና ጥራቱን በጠበቀ መንገድ ሊያስፋፉ ይችላሉ የሚል እምነት ስለአለ ነው..... ብለዋል ፡፡
ይቀጥላል

Read 4366 times