Saturday, 07 December 2013 11:13

“...ከቫይረሱ ነጻ የሆነ ትውልድን ለማፍራት ኃላፊነትን መጋራት

Written by  ፀሐይ ተፈረደኝ (ከኢሶግ)
Rate this item
(5 votes)

ሁሉም እርግዝና የተፈለገ መሆን አለበት፡፡
ሁሉም እርጉዞች በሰለጠነ የሰው ኃይል ሊወልዱ ይገባል፡፡
ሁሉም ጨቅላ ሕጻናት በህክምና ባለሙያ ሊወለዱ ይገባል፡፡
ሁሉም ሴቶች በራሳቸውም ይሁን በልጆቻቸው ጤና ላይ ..በእርግዝና ፣መውለድ እና ከወሊድ በሁዋላ.. ችግር

ሲገጥማቸው በስራ ላይ ያለ እና የተሟላ አገልግሎት የሚሰጥ የህክምና ተቋም በቅርባቸው እና በቀላሉ ሊያገኙ

የሚችሉበት መንገድ መመቻቸት አለበት፡፡
ጥንቃቄ የተደረገለት እርግዝና፣ ልጅ መውለድ እና እናትነት መሰረታዊ የሰብአዊ መብት ነው፡፡
ከላይ ያነበባችሁት የዘንድሮውን የአለም የኤችአይቪ ኤይድስ ቀን ምክንያት በማድረግ የአለም የጤና ድርጅት ድህረገጽ

ለንባብ ያበቃው ነው፡፡ የአለም ኤችአይቪ ቀን ህዳር 22/ 2006 ዓ/ም ተከብሮ የዋለ ሲሆን የዚህ ቀን በየአመቱ መከበር

አላማም ሀገራት እንዲሁም ህዝቦች በየጊዜው የበሽታውን አሳሳቢነት በመገንዘብ የአሰራር ስልቶቻቸውን እያሻሻሉ

ስለእውነታው በግልጽ እየተወያዩ ህዝብን ከበሽታው ስርጭት ማዳንና ለወደፊቱ ከቫይረሱ ነጻ የሆነ ትውልድን

ለማፍራት ነው፡፡
የአለም ኤችአይቪ ኤይድስ ቀን የዘንድሮው መሪ ቃል “Shared responsibility: Strengthen Results for an AIDS

– Free Generation.”  የሚል ነው፡፡ ሀላፊነትን መጋራት እና ከቫይረሱ ነጻ የሆነ ትውልድን ማፍራት የአለም ሀገራት

ሊያተኩሩበት የሚገባ ትልቅ የስራ ድርሻ መሆኑን እ.ኤ.አ የ2013/ የኤድስ ቀን መሪ ቃል ያሳስባል፡፡
የአለም ኤድስ ቀን መከበር የጀመረው እ.ኤ.አ ከ1988 /ማለትም ከዛሬ 25/ አመት ጀምሮ ሲሆን ሀሳቡን ያፈለቁትም

እ.ኤ.አ በ1987/ James W.Bunn & Thomas Netter የተባሉ በጊዜው በአለም የጤና ድርጅት ውስጥ በጄኔቭ

ኤይድስን በሚመለከት መረጃን ለህዝብ ያደርሱ የነበሩ ናቸው፡፡ እነዚህ ሁለት ሰዎች ሀሳባቸውን ዛሬ UNAIDS

በሚባለው መስሪያ ቤት በዚያን ጊዜ የአለም አቀፉን ፕሮግራም ለሚመሩት Dr. Jonatahan Mann  ዲሴምበር 1

/የአለም አቀፍ የኤይድስ ቀን ተብሎ ሊታሰብ ይገባል ባሉት መሰረት ሀሳባቸው ተቀባይነትን አግኝቶ እነሆ በመከበር ላይ

ይገኛል፡፡
የአለም የጤና ድርጅት  ድህረ ገጽ እንደሚገልጸው እ.ኤ.አ በ2009 ወደ 400.000 የሚሆኑ ህጻናት አዲስ በቫይረሱ

መያዛቸውን እና ከዚህም ወደ 90 ኀ ከሰሀራ በታች ባሉ ሀገራት ከእናት ወደ ልጅ በመተላለፍ ነው፡፡ ኤችአይቪ ቫይረስ

ከእናት ወደ ልጅ እንዳይተላለፍ አስፈላገው ስራ ካልተሰራ ከ20 -45% የሚሆኑት የሚወለዱ ልጆች በቫይረሱ ሊያዙ

የሚችሉ ሲሆን ከነዚህም አብዛኞቹ የሁለተኛውን አመት የልደት በአላቸውን ሳያከብሩ ህይወታቸው ያልፋል፡፡ ከዚህም

በላይ በቫይረሱ ከተያዙት እርጉዝ ሴቶች 42ቴ000-60ቴ000 የሚሆኑት ለህልፈት ይዳረጋሉ፡፡ ይህ መረጃ

የሚያመለክተው ባላደጉት ሀገራት በተለይም ከሰሀራ በታች ባሉ የአፍሪካ ሀገራት ያለውን እውነታ ሲሆን የበለጸጉት

ሀገራት እውነታ ግን በፍጹም ከዚህ የተለየ ነው፡፡ ባደጉት አገራት አዲስ በቫይረሱ የሚያዙ ህጸናት እና በቫይረሱ

ምክንያት የሚሞቱ እናቶች ቁጥር ወደ ዜሮኀ  ወርዶአል፡፡ ስለዚህም ህጻናቱ በቫይረሱ እንዳይያዙ እና እናቶችም

በቫይረሱ እንዳይጎዱ ማድረግ ይቻላል ይላል የአለም የጤና ድርጅት መረጃ፡፡ በ2015 / በአፍሪካ ከሚጠበቁት የልማት

ግቦች መካከል የእናቶችና የህጻናት ጤንነት መሻሻል የሚገኝበት ሲሆን በተለይም ከኤችኤይቪ ጋር በተያያዘ ሁለት

መሰረታዊ ነጥቦችን ያካተተ ነው፡፡
አዲስ በቫይረሱ የሚያዙ ህጻናትን ቁጥር በ2009 /ከተመዘገበው በ90 ኀ ያህል መቀነስ
ከኤችአይቪ ኤድስ ጋር በተያያዝ የሚከሰቱ የእናቶችን ሞት በ50%  መቀነስ የሚሉ ናቸው፡፡
ከላይ የተገለጸው መረጃ አለም አቀፍ ገጽታ ያለው ሲሆን በኢትዮጵያ ከኤችአይቪ ኤይድስ ጋር በተዛመደ ሜይ 30/2013

የወጣ መረጃ የሚከተሉትን  እውነታዎችን ያሳያል፡፡
የኢትዮጵያ ሕዝብ ብዛት ወደ 86/ ሚሊዮን የሚጠጋ ሲሆን በየአመቱ እንደሚገመተው ከቫይረሱ ጋር የሚኖሩ ሰዎች ወደ

759ቴ268 ይጠጋል፡፡ ከዚህም ውስጥ ከቫይረሱ ጋር የሚኖሩ እርጉዝ ሴቶች ቁጥር ወደ 34ቴ524 ይደርሳል፡፡
የኤችአይቪ ስርጭትን በሚመለከት መረጃው እንደሚጠቁመው ባብዛኛው በእድሜያቸው ከ15-24 የሚደርሱ ወጣቶች

በቫይረሱ እንደሚያዙ ነው፡፡ትልልቅ ሰዎችን በሚመለከት 1.5% ያህል በቫይረሱ የሚያዙ ሲሆን ከነዚህም ውስጥ ወንዶች

1% ሴቶች ደግሞ 1.9 % ይሆናሉ፡፡ የኤችኤቪ ቫይረስ ስርጭት 2.4 % ያህሉ እርጉዝ ሴቶችን የሚመለከት ነው፡፡
ኤችአይቪ ቫይረስ ከእናት ወደልጅ እንዳይተላለፍ ለማድረግ በኢትዮጵያ በመሰራት ላይ ያለውን ተግባር የሚመለከተው

ይህ የመረጃ ገጽ እንደሚጠቁመው ወደ 33.4% የሚሆኑ እርጉዝ ሴቶች የኤችአይቪ ምርመራ ያደረጉ ሲሆን ጸረ

ኤችአይቪ መድሀኒትን በመጠቀም ረገድ በ2012/ ወደ 41% ያህል እንደሚደርሱ ተጠቁሞአል፡፡ በኢትዮጵያ ከቫይረሱ ጋር

ለሚኖሩ እርጉዝ እናቶች የጸረ ኤችአይቪ መድሀኒት ሽፋን እስከ 45% የሚደርስ መሆኑም ተገልጾአል፡፡ ከእናት ወደልጅ

ቫይረሱ የመተላለፉ ሁኔታን መረጃው እንደሚጠቁመው በ2011/ ወደ 30% ያህል ሲሆን በ2012 ደግሞ ወደ 20% ዝቅ

ብሎአል፡፡ ስለዚህም የህክምናው ክትትልና የህብረ ተሰቡ ንቃተ ህሊና ባደገ እና በጨመረ ቁጥር ከቫይረሱ ነጻ የሆነ

ትውልድን የማፍራት ሂደቱ በተወሰነለት የጊዜ ገደብ ተግባራዊ እንደሚሆን ይጠበቃል፡፡
እ.እ.አ 2013/ ዲሴምበር 1/ የተከበረውን ኤችአይቪ ኤይድስ ቀን ምክንያት በማድረግ የወጡ የተለያዩ መረጃዎች

እንደሚጠቁሙት...
በተለያዩ የአለማችን ክፍሎች ኢትዮያን ጨምሮ ወደ 9.7 ሚሊዮን ሰዎች ፀረኤችአይቪ መድሀኒት ተጠቃሚ ሆነዋል፡፡
እ.ኤ.አ በ1981 እና 2007/መካከል ኤይድስ 25 ሚሊዮን ሰዎችን ለህልፈት ዳርጎአል፡፡
በ2012/በአለም ወደ 35.3 ሚሊዮን ሰዎች ከቫይረሱ ጋር እንደሚኖሩ ይገመታል
ከሰሀራ በታች ያሉ ሐገራት ሕዝቦች ይበልጡን በቫይረሱ እንደሚጎዱ የታወቀ ሲሆን ከ20 ሰዎች መካከል አንዱ

በቫይረሱ እንደሚያዝ ይገመታል፡፡
በአለማችን ከቫይረሱ ጋር ከሚኖሩ ሰዎች  ወደ 69% የሚሆኑት ከሰሀራ በታች ባሉ ሀገራት የሚገኙ ናቸው፡፡
ኤችአይቪ ለጊዜው ጭርሱንም ባይድንም ነገር ግን በህክምና እና በአኑዋኑዋር ዘዴ ሊረዳ የሚችል ነው፡፡
የተለያዩ መረጃዎች ለንባብ ካበቁዋቸው እውነታዎች የሚከተሉት ይገኙበታል፡፡
እ.ኤ.አ በ2012 ዓ/ም 35.5/ ሚሊዮን ሰዎች በአለም አቀፍ ደረጃ ከቫይረሱ ጋር እንደሚኖሩ ታውቆአል፡፡ የቫይረሱ

ስርጭት ከጀመረበት ጊዜ ጀምሮ ወደ 75/ ሚሊዮን የሚሆኑ ሰዎች በቫይረሱ ተይዘዋል፡፡
አዲስ በኤችአይቪ ቫይረስ የሚያዙትን በሚመለከት መረጃው እንደሚጠቁመው
እ.ኤ.አ ከ2001 ወዲህ በ33% ቀንሶአል፡፡
በአለም አቀፍ ደረጃ 2.3 ሚሊዮን ሰዎች በቫይረሱ የተያዙ አዲስ ሰዎች የተመዘገቡ ሲሆን ይህም ቀደም ሲል ከነበረው

ዝቅ ብሎ የሚገኝ ነው፡፡
በአደጉ እና በታዳጊ ሰዎች ላይ የቫይረሱ መከሰትን በሚመለከት ከ26/ በሚበልጡ ሀገራት እንደታየው በ2001 እና 2012

መካከል በ50% መቀነሱ ተመዝግቦአል፡፡
ከቫይረሱ ጋር በተያያዘ የሚከሰት ሞትን በሚመለከት
እ.ኤ.አ በ2005 ከተመዘገበው 30% ያህል ቀንሶ ይገኛል፡፡
በ2012/ ወደ 9.7 ሚሊዮን ከቫይረሱ ጋር የሚኖሩ ሰዎች ጸረ ኤችአይቪ መድሀኒት ተጠቃሚ የሆኑ ሲሆን ይህም በማደግ

ላይ ባሉ ሀገራትና በመካከለኛ ደረጃ ባሉ ሀገራት ነው፡፡ ከነዚህ 61 ኀ የሚሆኑት ተጠቃሚ የሆኑት በ2010 /የአለም

የጤና ድርጅት ባወ ጣው መመሪያ መሰረት ሲሆን 34% የሚሆኑት ሰዎች ደግሞ ተጠቃሚ የሆኑት አሁ ንም የአለም

የጤና ድርጅት በ2013/ባወጣው መመሪያ መሰረት ነው፡፡
ከኤችአይቪ ቫይረስ ጋር የሚኖሩ ሰዎች ከቲቢ በሽታ ጋር በተያያዘ የሚኖረው ሞት ከ2004/ጀምሮ ወደ 36% ቀንሶ

ተመዝግቦአል፡፡  ቲቢ አሁንም በኤይድስ ቫይረስ የተያዙ ሰዎችን ለሞት በማብቃት ቀዳሚውን ስፍራ ይይዛል፡፡
 አለም አቀፉ መድረክ እንደተስማማበት እ.ኤአ እስከ 2015 ድረስ ከእናት ወደልጅ የሚተላለፈው ኤችአይቪ ቫይረስ እና

እናቶች በቫይረሱ ምክንያት መሞታቸው እንዲቀንስ ማስቻል ነው፡፡ ኢትዮጵያም በዚህ ስምምነት መሰረት ፕሮግራሙን

ተቀብላ ህዝቦችዋን ለማዳን ያላሰለሰ ጥረት በማድረግ ላይ መሆኑዋ እሙን ነው፡፡ የኢትዮያ የጽንስና ማህጸን ሐኪሞች

ማህበር በበኩሉ በተለያዩ መስተዳድሮች አዲስ አበባን ጨምሮ ከግል የህክምና ተቋማት ጋር በመሆን ኤችአይቪ ከእናት

ወደልጅ እንዳይተላለፍ የሚያስችለውን ፕሮጀክት ካለፉት አራት አመታት ወዲህ በማስፈጸም ላይ ይገኛል፡፡ ከቫረሱ ነጻ

የሆነ ትውልድን ለማፍራት አጋር ድርጅቶችም የበኩላቸውን እገዛ በማድረግ ላይ ናቸው፡፡ 

Read 3690 times