Saturday, 14 December 2013 13:06

ማንዴላንአትመልስም!

Written by 
Rate this item
(5 votes)

“የታሪክህ አፅም
ተቆፍሮ ቢወጣ፤
ቀን የጣላት፣ ዘውድ ናት
የደፋሃት ባርኔጣ
የማንነትህ ዙፋን ነው
በርጩማህንም ነፃ አውጣ፣
ሥርወ - ቤትህን አውጅ
ጐጆህ ሀገር ትውጣ
ሳትነግሥ እንዳትሞት
አንጋለህ ሳትቀጣ
ብድርህን ሳትመልስ
ወግረህ ሳትቆጣ”
…እያለ ከሚያዝህ
ከዚያ ውዥንብር መንፈስ፣
ቀልብያህ ሳትድን
ነፍስህ ሳትፈወስ፣
ማንዴላን አታንሳ
ትርጉም ለማልፈስፈስ፡፡
ከተጠናወተህ፤ ስም አይጠሬ ህመም
የትውልድ በሽታ፣
ከሚያስደረድርህ፤ ጠመንጃና መውዜር
በበገና ፈንታ፣
አረር ከሚያስጤስህ
ከከርቤ እያፋታ፣
ጐጆ ከሚያስመልክ
ሀገር እያስረታ፤
ታሞ ካሳመመህ
ከይሄ ርኩስ መንፈስ፣
ቀልብያለህ ሳትድን
ነፍስህ ሳትፈወስ
ሕዋ ያህል ቃልን
በጐጆ አፍ ማወደስ
የጀግናውን ገድል
ትቢያ ላይ መለወስ፡፡

ሳምሶን ጌታቸው ተ.ሥ  

Read 2962 times