አድረን ልንገናኝ….
ነግቶ ልትመጪልኝ….
ለአንድ ቀን ባጣሁሽ፣
በዚሁ ቀን ብቻ - ብዙ ቀን ናፈኩሽ፡፡
ማዕድኑ ሰው
እግዜር አመዛዝኖ፣
ከአፈሩ ዘግኖ፣
መሬት ላይ በትኖ…
‹‹ሰው ሁን›› ካለው ወዲህ…
መኖር ያልደፈረ…
መሞት ያልጀመረ…
ለአንዱም ያልበቃ፣
በአንዱም ያልነቃ፣
ስንት አለ ጥሬ ዕቃ!?
የሴት ልጅ ነኝ
የሴት ልጅ መባሌ - ቂም አያስይዘኝም፣
ምክንያቱም አባቴ - አላረገዘኝም፡፡
በገጣሚ ሲሳይታደሰ /ዘ-ለገሐሬ/
Published in
የግጥም ጥግ