Monday, 14 April 2014 10:37

‹‹የኔታ›› ድራማ ኮሜዲ ፊልም ሰኞ ይመረቃል

Written by 
Rate this item
(2 votes)

“አንድ ቀን” የቤተሰብ ፊልም በቅርቡ ለተመልካች ይቀርባል

በደራሲ፣ዳይሬክተርና ፕሮዱዩሰር አለማየሁ ታደሰ እንዲሁም በኤክስኪዩቲቭ ፕሮዱዩሰር ማርታ ጌታቸው የተዘጋጀው ‹‹የኔታ›› የተሰኘ ድራማ ኮሜዲ ፊልም፤ የፊታችን ሰኞ በ11 ሰዓት በብሔራዊ ትያትር ይመረቃል፡፡ በፊልሙ ላይ ራሱ አለማየሁ ታደሰን ጨምሮ  ኮሜዲያን ደረጄ ሀይሌ፣ ቃልኪዳን ጥበቡ፣ አስናቀ ንጉሴ፣ማርታ አሰፋ እና ሌሎች ተዋንያን ተሳትፈውበታል፡፡
በሌላ በኩል በደራሲና ፕሮዲዩሰር ሜላት ነብዩ እና በዳሬክተር ቢኒያም ወንድይፍራው የተዘጋጀው “አንድ ቀን” የተሰኘ የቤተሰብ ፊልም፣ ሚያዚያ 23 ከቀኑ በ11 ሰዓት በጣይቱ ጃዝ አምባ አዳራሽ  የሚመረቅ ሲሆን በቅርቡ ለተመልካች ይቀርባል ተብሏል፡፡
በሜሊያም መልቲ ሚዲያ ፕሮዳክሽን በተሠራው በዚህ ፊልም ላይ ወጣትና አንጋፋ ተዋንያን  የተሳተፉበት ሲሆን ፊልሙን ለማጠናቀቅ አንድ ዓመትና ከ500ሺ ብር በላይ እንደፈጀ አዘጋጆቹ ተናግረዋል፡፡

Read 4206 times