Saturday, 26 April 2014 12:14

የከፍተኛ መኮንኖችን ጡረታ በ5 ዓመት ማራዘም ተፈቀደ

Written by 
Rate this item
(5 votes)

“ቦርድ” ለሚወጡ ወታደሮች የ2 በመቶ ክፍያ ተጨመረ

የመከላከያ ሚኒስቴር እንደአስፈላጊነቱ እያየ የጦር መኮንኖችን የአገልግሎት ዘመንና የጡረታ መሰናበቻ እድሜ በሁለት ዓመት ለማራዘም የነበረው ሥልጣን እንደተሻሻለ ምንጮች ገለፁ፡፡ የመከላከያ ኃይል አባላት የሥራ ዘመናቸውን በ3 ወይም በ5 ዓመት ማራዘም በአዲሱ አሰራር ተፈቅዷል፡፡ የጡረታ እድሜ በ5 ዓመት የሚራዘመው ለከፍተኛ መኮንኖች እንደሆነ ምንጮች ጠቅሰው፤ ከከፍተኛ መኮንን በታች ደግሞ ካሁን ቀደም የነበረው የሁለት ዓመት ማራዘሚያ ወደ ሶስት አመት ከፍ እንዲል መደረጉን ገልፀዋል፡፡
ከዚሁ የጡረታ ማራዘምያ አዲስ አሰራር ጋር፤በ“ቦርድ” ለሚሰናበቱ የመከላከያ ኃይል አባላት የሁለት በመቶ ክፍያ ተጨምሯል፡፡ የመከላከያ ሠራዊት አባል በተለያዩ ምክንያቶች “ቦርድ” እንዲወጣ ሲወሰን፣ ወርሃዊ ክፍያው የደሞዙ አርባ አምስት በመቶ የነበረ ሲሆን አሁን አርባ ሰባት በመቶ እንዲሆን ተወስኗል፡፡

Read 3518 times