Print this page
Saturday, 26 April 2014 13:02

የግጥም ጥግ

Written by 
Rate this item
(8 votes)

ዝም ብንል ብናደባ
ዘመን ስንቱን አሸክሞን፤
የጅልነት እኮ አይደለም
እንድንቻቻል ነው ገብቶን፡፡
 ባለቅኔ ሎሬት ጸጋዬ ገ/መድኅን
ቅልስልሱ ይሁዳ
ይሁዳማ ቅልስልስ ነው
አቅፎና ደግፎ
ክርስቶስን ሰጠ
ለሞት አሳልፎ፤
የኛ ዘመን ሰው ግን
ሰቅሏችሁ ሲያበቃ
በፈገግታ ክቦ፤
አቅፎ ይስማችኋል
አይኑን በጨው አጥቦ፡፡
                                       አማኑኤል  መሀሪ
ስሙነኛ ስንኝ
የህዝቦች ልቦና
በታሪክ አንደበት፤
‹‹ንጉሥ ነህ!!›› ባለ አፉ
የሆሳዕና ለት፤
‹‹ስቀለው!!!›› ይልሀል
ውሎ አድሮ እንደ ዘበት፡፡
                                        ፈለቀ  አበበ                           


Read 3091 times
Administrator

Latest from Administrator