Monday, 19 May 2014 08:23

የቦኮ ሐራምና የአቡበከር ቁጣ፡ “የገደልነውና የጠለፍነውን ያህል አልተወራልንም”

Written by 
Rate this item
(3 votes)

“276 ሴት ተማሪዎች መጠለፋቸውን ብቻ ታወራላችሁ። በሦስት እጥፍ የሚበልጡ ተማሪዎችን ጠልፈናል። ሰሞኑን በአንድ ቦታ 300 ሰዎች ገድለናል። ለምን ይሄ አይወራም?”

   “አገር በቀል እውቀት” በሚል ሰበብ ስልጣኔን እያንቋሸሸ፤ አልያም የአሜሪካና የአውሮፓ የሳይንስ ትምህርትን እያብጠለጠለ፣ ኋላቀርነትን የሚሰብክ ፕሮፌሰርና ዶክተር ሞልቷል። ቦኮ ሐራም ከዚህ የተለየ አላማ የለውም። ስሙ ራሱ፤ “የምዕራባዊያን ትምህርት ሐራም ነው” እንደማለት ነው። ቦኮ ሐራም፤ ከወገኛ ምሁራን የሚለይበት ዋነኛ ባህርይው፤ ኋላቀርነትን በመስበክ ብቻ የሚመለስ አለመሆኑ ነው። ስብከቱን በተግባር ያሳያል። አዳሪ ትምህርት ቤት ውስጥ ገብቶ ከ50 በላይ ተማሪዎችን መግደል፤ የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ማዕከልን አቃጥሎ ደርዘኖችን መጨፍጨፍ፣ ሴት ተማሪዎችን መውሰድ... የሳይንስ ትምህርትን ከማንቋሸሽ አልፎ፤ ሳይንስ የሚያስተምሩና የሚማሩ ሰዎችን ያሳድዳል።

ቦኮ ሐራም በሚፈነጭበት ሰሜናዊ የናይጄሪያ አካባቢ፣ “276 ሴት ተማሪዎች መጠለፋቸውን ብቻ ታወራላችሁ። በሦስት እጥፍ የሚበልጡ ተማሪዎችን ጠልፈናል። ሰሞኑን በአንድ ቦታ 300 ሰዎች ገድለናል። ለምን ይሄ አይወራም?” የቦኮ ሐራምና የአቡበከር ቁጣ፡ “የገደልነውና የጠለፍነውን ያህል አልተወራልንም” የሽብር ፍርሃት ስለነገሰ ብዙዎቹ ትምህርት ቤቶች ተዘግተዋል። የአመቱ ፈተና እንዳያመልጣቸው በአንድ ትምህርት ቤት ለመሰባሰብ የደፈሩት ሴት ተማሪዎችም፤ ከቦኮ ሐራም አላመለጡም። ትምህርት ቤቱን በመውረር ነው 276 ሴት ተማሪዎችን የጠለፋቸው። ከወላጆችና ከቤተሰቦች እሮሮ ጋር የባኮ ሐራም ዝና በመላው አለም የገነነው፤ ከዚሁ ጠለፋ ጋር ተያይዞ ነው። ተቃውሞና ውግዘት ከየአቅጣጫው ከሁሉም የአለም ማዕዘናት ጐረፈ። የባኮ ሐራም አለቃ ነውጠኛው አቡባከር ባለፈው ሰኞ በቁጣ እየደነፋ ለአለማቀፉ እሪታ ምላሽ ሰጥቷል።

ውግዘት ስላበዛ አይደለም አቡበከር የተናደደው። “ጥፋት አልሰራሁም፤ ጥፋቴ ተጋነነ” የሚል አይደለም የአቡበከር ምላሽ። በተቃራኒው፤ “የሰራሁትን ነገር አሳነሳችሁብኝ” በማለት ቁጣውን የገለፀው አቡባከር፤ ከተወራለት የሚበልጥ ጠለፋና ግድያ እንደፈፀመ ድርጊቶቹን በመዘርዘር ተናግሯል። አለም ሁሉ የሚያወራው ስለተጠለፉት ሴቶች ብቻ መሆኑ አናድዶታል። በአመት ውስጥ በሶስት እጥፍ የሚበልጡ ታዳጊዎችን እንደጠለፍን ለምን ይዘነጋል? አለም ሁሉ ይህንን የ ማ ያ ወ ራ ው ለ ም ን ድ ነ ው ? በማለት ብስጭቱን ገልጿል አቡበከር። የተናደደው በዚህ ብቻ አይደለም። ቦካ ሐራም ሴት ተማሪዎችን ከመጥለፉ በፊትም ሆነ በኋላ የፈፀምኳቸው ብዙ “ጀብዱዎች” ቸል ተብለውብኛል ባይ ነው - አቡበከር። ከወር በፊት በናይጄሪያ ዋና ከተማ በአቡጃ የአውቶብስ መነሃሪያ ላይ ባደረሰው የፍንዳታ ጥቃት 71 ሰዎች ተገድሏል።

ይሄስ ለምን ተረሳ? ለምን አይወራም? አቡበከር በዚህ ሁሉ ይንገበገባል። በቅርቡ ከሳምንት በፊትም ቦኮ ሐራም በአንዲት ከተማ መስጊድ ውስጥ የተጠለሉ 300 ሰዎችን ጨፍጭፏል። ይሄም መነጋገሪያ መሆን እንዳለበት አቡበከር አሳስቧል። እውነትም፤ ቦኮ ሐራም፤ በአማካይ በየእለቱ 10 ናይጀሪያዊያን እየገደለ በሁለት ዓመታት ውስጥ ከሰባትሺ በላይ “ግዳይ” ጥሏል። በኋላቀር ባህልኮ ክብር እና ማዕረግ የሚገኘው “ስንት ሰው ገደለ?” በሚል ነው። አቡበከርም “ገዳዬ፣ ገዳዬ” እየተባለ እንዲዘፈንለት ቢጠብቅ አይገርምም። አለም ሌላ ሌላውን ሁሉ ትቶ፣ ስለ ተጠለፉት ሴቶች ብቻ ማውራቱን የሚቀጥል ከሆነስ? አቡበከር፤ ለዚህም ምላሽ አለው። ብዙዎቹ ሴት ተማሪዎች... ገና የ9 አመት፣ ቢበዛ የ12 አመት ታዳጊዎች ናቸው።

“ፈጣሪ ምስክሬ ነው፤ ገበያ አውጥቼ እሸጣቸዋለሁ። የ12 አመት... 9 አመት ልጃገረዶቹን ሁሉ ባል እንዲያገቡ አደርጋለሁ” ሲል ዝቷል - በቪዲዮ ባሰራጨው መልእክት። እስካሁን የተወሰኑት ልጃገረዶች በ12 ዶላር እየተሸጡ ሚስት ለመሆን እንደተገደዱም ተዘግቧል። አቡበከር፤ ለናይጄሪያውያን ያስተላለፈው መልእክት የእልቂት አርአያነቱን እንዲከተሉ የሚጋብዝ ነው። “ሳታመነቱ ገጀራችሁን ጨብጣችሁ ተነሱ። በየቤቱ ሰብራችሁ እየገባችሁ ግደሉ። ያገኛችሁትን ሰው ሁሉ እዚያው በተኛበት ግደሉ” ብሏል - አቡበከር።

Read 3703 times