Saturday, 07 June 2014 13:48

ዘመናዊ የህፃናት አስተዳደግ ስልጠና የወሰዱ ሞግዚቶች ተመረቁ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

ህፃናት አካላዊና አዕምሮአዊ ጤንነታቸው ተጠብቆ የሚያድጉበትን መንገድ የሚያመቻችና በህፃናት አያያዝ፣ አመጋገብ እንዲሁም የህፃናትን ባህርይ በመረዳትና በመንከባከብ ላይ ያተኮረ ዘመናዊ የህፃናት አስተዳደግ ስልጠና የወሰዱ 55 ሞግዚቶችን ማስመረቁን “እሹሩሩ” የሞግዚቶች ማሰልጠኛ ተቋም አስታወቀ፡፡
ድርጅቱ ለመጀመሪያ ጊዜ አሰልጥኖ ያስመረቃቸው እነዚሁ ሞግዚቶች፤ በህፃናት እንክብካቤና አስተዳደግ ላይ በቂ እውቀት ኖሮአቸው፣ ህፃናቱን በአግባቡ ለማሳደግ የሚያስችላቸውን ሥልጠናና እውቀት ያገኙ መሆናቸው ተገልጿል፡፡ በህፃናት አስተዳደግ ላይ ጥናት አካሂደው ወደ ሥራው መግባታቸውን የሚናገሩት የድርጅቱ ኃላፊዎች፤፤ በአገራችን ህፃናትን የሚንከባከቡ ሞግዚቶች በእውቀት የታገዘ ልምድ ስለሌላቸውና ሳይንሳዊ የሆነ ሥልጠና ስለአልወሰዱ በህፃናቱ አስተዳደግና የወደፊት ህይወት ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ማሳደራቸውን ገልፀዋል፡፡ ይህንን ችግር ለመቅረፍም ሞግዚቶቹን አሰልጥነው ወደ ሥራ ለመሠማራት ማቀዳቸውንና የመጀመሪያ ዙር ሰልጣኞችን ማስመረቃቸውንም ገልፀዋል፡፡

Read 2882 times