Print this page
Saturday, 07 June 2014 14:03

የዝነኛ ደራስያን አስገራሚ እውነታዎች

Written by 
Rate this item
(4 votes)

በወንጀል ምርመራ ታሪኮች ላይ ባተኮሩ የልብወለድ ሥራዎቿ የምትታወቀው እንግሊዛዊቷ ደራሲ አጋታ ክርስቲ፤ ከ2 ቢሊዮን በላይ መፃህፍቶቿ ተቸብችበውላታል፡፡ የመጀመሪያ ሥራዋ The Mysterious Affair at Styles እ.ኤ.አ በ1920 ዓ.ም የታተመላት ሲሆን And Then There Were None የተባለው ሥራዋ 100 ሚሊዮን ቅጂዎች እንደተሸጡላት መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡
ከ60 በላይ በወንጀል ምርመራ ላይ የሚያጠነጥኑ ልብወለዶች የፃፈችው አጋታ ክርስቲ፤ 14 የአጭር ልብወለድ መድበሎች ያሳተመች ሲሆን ከ12 በላይ የመድረክ ትያትሮችንም ጽፋለች፡፡ በብዛት በመታተም ከሼክስፒርና ከመጽሐፍ ቅዱስ ቀጥሎ በ3ኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች፡፡ በዓለም ላይ ለረዥም ጊዜ በመድረክ ላይ በመቆየት የአጋታን ትያትር የሚወዳደር የለም፡፡ The Mousetrap የተሰኘው ትያትሯ እ.ኤ.አ ከ1952-2012 ዓ.ም ከመድረክ ሳይወርድ ታይቶላታል፡፡ ለ60 ዓመት ገደማ ማለት ነው፡፡
በልብወለድ መፃሕፍቷ ላይ ተመስርተው የተሰሩ ከ30 በላይ ፊቸር ፊልሞች ያሉ ሲሆን ወደ ቴሌቪዥን፣ ሬዲዮ፣ ቪዲዮ ጌምና ኮሚክ መፃህፍት የተቀየሩ በርካታ ስራዎችም አሏት፡፡ ስድስት የፍቅር ልብወለድ መፃሕፍትን ሜሪ ዌስትማኮት በሚል የብዕር ስም ያሳተመችው ደራሲዋ፤ ስራዎቿ ከ100 በሆኑ በላይ ቋንቋዎች ተተርጉመውላታል፡፡
በከፍተኛ ሽያጭና ተወዳጅነት የምንጊዜም ምርጥ ደራሲ የሚል ክብርና ሞገስ የተቀዳጀችው አጋታ፤ ከግማሽ ክ/ዘመን በላይ የፃፈች ሲሆን የእሷን ሥራዎች ማንበብ ዓለምአቀፍ የጊዜ ማሳለፊያ ተደርጐ እስከመቆጠር ደርሷል፡፡ ቁጥራቸው ጥቂት የማይባሉ የአጋታ ሥራዎች ወደ አማርኛ ተተርጉመው ለኢትዮጵያውያን ተደራሲያን መቅረባቸው ይታወቃል፡፡

Read 3247 times
Administrator

Latest from Administrator