Print this page
Saturday, 07 June 2014 14:35

የአለም ዋንጫ ቁማር ከ30 ቢ. ዶላር በላይ ነው

Written by 
Rate this item
(0 votes)

   በእያንዳንዱ ጨዋታ ላይ ለቁማርና ለውርርድ የሚከፈለው ገንዘብ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መጥቷል። በአለም ዋንጫ ውድድሮች ላይ በየጨዋታው በቢሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ ለቁማር እየዋለ መሆኑን የዘገበው ዘ ኢኮኖሚስት፣ በአጠቃላይ ከ30 ቢ. ዶላር በላይ ገንዘብ የቁማር መጫወቻ እንደሚሆን አመልክቷል።
የለንደን ህገወጥ ሬዲዮ ጣቢያዎች እያበቃላቸው ይሆን?
በሃያኛው ክፍለዘመን’ኮ ያልተበላሸ አገር የለም ማለት ይቻላል። “የግለሰብ መብት” እና “የነፃ ገበያ ስርዓት” የተወለዱባት እንግሊዝ ሳትቀር፣ ቀስ በቀስ ከስልጣኔ ማማ ቁልቁል መንሸራተት አልቀረላትም ነበር። መንግስት፣ የግል ኩባንያዎችን እንዲወርስ ባይደረግም፤ ካሳ እየከፈለ የተወሰኑ ድርጅቶችን ወደ መንግስት ይዞታነት ሲያዛውር አልነበር? በዚያ ላይ የግል ሬድዮና ቴሌቪዥን ጣቢያዎች በብዛት እንዳይቋቋሙ በህግ ታግደው ነበር። በዚህ ምክንያት ነው፤ በርካታ የሬዲዮ ጣቢያዎች በድብቅ መስራት የጀመሩት።
የመንግስት ሪፖርት እንደሚገልፀው፣ በለንደን ውስጥ 75 ያህል ድብቅ የሬዲዮ ጣቢያዎች አሉ። ከእነዚህ “ህገወጦች” መካከል አስሩ ጣቢያዎች፣ የ24 ሰዓት ስርጭት ያስተላልፋሉ። አንዳንዶቹ ደግሞ፣ ለበርካታ አመታት ያለማቋረጥ የሰሩ ናቸው። ዛሬ ዛሬ ግን፣ ቀስ በቀስ እየተዳከሙ ህልውናቸው እያበቃለት ይመስላል። ጣቢያዎቹ የተዳከሙት በመንግስት ቁጥጥርና ክትትል ሳቢያ አይደለም።
በእርግጥ “ህገወጥ” ስለሆኑ፤ አድራሻቸውን አጥፍተው በድብቅ ካልሰሩ በቀር መዘጋታቸውና መቀጣታቸው አይቀርም። የማሰራጫ አንቴናቸውን የሚተክሉት በድብቅ ነው። ከስቱዲዮ ወደ አንቴና የሬዲዮ ስርጭት የሚያስተላልፉትም በጥንቃቄ ነው - ለቁጥጥር በማያመች ጨረር አማካኝነት። ነገር ግን፣ የመንግስት ባለስልጣናትም፣ “ህገወጥ” የሬዲዮ ጣቢያዎችን አሳድደው ለመያዝ የአሰሳ ዘመቻ አያካሂዱም። ክትትልና ምርመራ ለማካሄድ ጊዜና ገንዘብ አያባክኑም። ለድብቅ ጣቢያዎች፣ “ህጋዊ እውቅና መንፈግ በቂ ነው” ብለው ያስባሉ - ባለስልጣናት። በአጭሩ፣ ጣቢያዎቹን ያዳከማቸው ወይም ስጋት ላይ የጣላቸው መንግስት አይደለም። ቴክኖሎጂ እንጂ።
ዘመኑ የኢንተርኔት ዘመን ነው። የፅሁፍ፣ የምስል፣ የድምፅና የቪዲዮ መልእክቶችን በቀላሉ በኢንተርኔት ማሰራጨትና መለዋወጥ ይቻላል። እገዳና ክልከላ ስለሌለ፣ ድብቅነትና ህገወጥነትም አያስፈልገውም። እናም አብዛኞቹ ድብቅ የሬዲዮ ጣቢያዎች፣ ስርጭታቸውን ወደ ኢንተርኔት ማዞር ጀምረዋል።  

Read 2374 times
Administrator

Latest from Administrator