Saturday, 21 June 2014 13:47

ጃኪ ጎሲ ከሄኒከን ጋር 1 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር ሊፈራረም ነው

Written by 
Rate this item
(13 votes)

‘ሰላ በይልኝ’ በሚለው ነጠላ ዜማው ከህዝብ ጋር ተዋወቀው ድምጻዊ ጃኪ ጎሲ፣ የሙዚቃ ኮንሰርት ለማቅረብ ከታዋቂው የቢራ አምራች ኩባንያ ሄኒከን ጋር የአንድ ነጥብ አምስት ሚሊዮን ብር ስምምነት ሊፈራረም ነው፡፡
አድማስ ሬዲዮ ከአትላንታ እንደዘገበው፣ ወጣቱ ድምጻዊ ጃኪ ጎሲ ከሰሞኑ ከሄኒከን ጋር ያደርገዋል ተብሎ የሚጠበቀው ይህ ስምምነት በአዲስ አበባ ከተማ ለሚከናወን የሙዚቃ ኮንሰርት ነው፡፡ የሙዚቃ ኮንሰርቱ የሚቀርብበትን ትክክለኛ ጊዜ መናገር ባይቻልም ለመጪው የኢትዮጵያውያን አዲስ አመት ዋዜማ ሊሆን እንደሚችል ዘገባው ጨምሮ ገልጧል፡፡
በተለያዩ የአሜሪካ ግዛቶችና የዓለም አገራት እየተዘዋወረ የሙዚቃ ኮንሰርቶችን በስፋት እያቀረበ የሚገኘው ድምጻዊው፣ ከወራት በፊት ከዝግጅት ክፍላችን ጋር ባደረገው ቃለ ምልልስ በአገር ውስጥም የሙዚቃ ኮንሰርቶችን ማዘጋጀት ዕቅድ እንዳለው መናገሩ ይታወሳል፡፡

Read 5510 times