Saturday, 21 June 2014 14:51

የብራ መብረቅ በናይጀሪያ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

ቦኮ ሃራም ባጠመደው ቦንብ 21 ወጣቶች ሲሞቱ፤ 27ቱ ቆስለዋል

ናይጀሪያውያን የእኛን ቡድን በደርሶ መልስ ጨዋታ አሸንፎ ለ20ኛው የአለም ዋንጨ ባለፈው የአፍሪካ ሻምፒዮን ብሔራዊ ቡድናቸው በእጅጉ ደስተኞች በመሆናቸው የብራዚሉ የአለም ዋንጫ እስኪጀመር በጣም ቸኩለው ነበር፡፡
አብዛኞቹ ናይጀሪያውንም ቡድናቐው ተካፋይ የሆነበት የብራዚሉ የአለም ዋንጫ,ኧ እስከ ፍፃሜው ድረስ (ያለው የአንድ ወር ጊዜ በየአደባባዩ ተሰብስበው የሚዝናኑበት አሪፍ የፌሽታ ጊዜ እንደሚሆንላቸው ሙሉ እምነት ነበራቸው፡፡
የሰሜን ምስራቅ ግዛቶች ውስጥ በሚኖሩት ናይጀሪያውያን ዘንድ ግን ይህን መሰሉ ስሜት ብዙም አልቆየም፡፡ ፅንፈኛ እስላማዊ አሸባሪ ቡድን የሆነው ቦኮ ሃራም በዋናነት ይንቀሳቀስበታል በሚባለው በዚህ አካባቢ የዓለም ዋንጫን መመልከት የታገደው ከጨዋታው ቀደም ብሎ ነው፡፡ ቦኮ ሀራም በዮቤና በአዳማዊ ግዛቶች “አዳሜ ሁሉ የአለም ዋንጫ ውድድርን በአደባባይ ተሰብስቤ እየጨፈርኩ በቴሌቪዥን እከታተላለሁ ስትል ውርድ ከራሴ!” በማለት በበራሪ ወረቀት የሰጠው ማስጠንቀቂያ ብዙዎችን ከፍ ያለ ስጋት ውስጥ መጣሉ አልቀረም፡፡
በእግር ኳስ ፍቅር ልባቸው ክፉኛ የነደደ በርካታ ናይጀሪያውያን ግን ስጋታቸውን እንደያዙም ቢሆን ሰብሰብ ብለው እየጨፈሩ ውድድሩን ከመመልከት ወደኋላ አላሉም፡፡ የዮቤ ግዛት የዳማቱሩ ከተማ ነዋሪ የሆኑ እግር ኳስ አፍቃሪ ናይጀሪያውያን ባለፈው ማክሰኞ ያደረጉትም ይህንኑ ነበር፡፡
ለቦኮ ሀራም ግን የእነዚህ ናይጀሪያውያን ድርጊት ማስጠንቀቂያን ቸል የማለት ተራ ስህተት ሳይሆን በሞት የሚያስቀጣ ከፍተኛ ወንጀል ነበር፡፡ እናም የቅጣት ቦምብ ተጠመደላቸው፡፡ ባለፈው ሳምንት ብራዚልና ሜክሲኮ እየተጫወቱ ሳለ ማንም ባላሰበውና ባልጠበቀው ሁኔታ የተጠመደው ቦምብ ድንገት ፈነዳ፡፡ አገር ሰላም ብለው ጨዋታውን በመከተተል ላይ ከነበሩት ወጣቶች መካከል ሃያ አንዱ ወዲያውኑ ሲሞቱ፤ ሃያ ሰባቱ የሚሆኑት ደግሞ ቀላልና ከባድ ጉዳት ደረሰባቸው፡፡ ብዙዎችን ድንጋጤ ውስጥ የከተተ የብራ መብረቅ!

Read 1959 times