Saturday, 21 June 2014 15:00

አርቲስት ይገረም ደጀኔ የመዝሙር ሲዲ አወጣ

Written by 
Rate this item
(2 votes)

“በሰው ለሰው” ድራማ የአዱኛን ገፀ - ባህሪ ወክሎ በመጫወት እና በበርካታ ስራዎቹ አድናቆትን ያተረፈው አርቲስት ይገረም ደጀኔ፤ “ቆምኩኝ ለምስጋና” የተሰኘ የምስጋና የመዝሙር ሲዲ ያወጣ ሲሆን፤ ሰኞ ገበያ ላይ እንደሚውል ተገለፀ፡፡ አርቲስቱ ለመዝሙሩ ከተከፈለው 40ሺህ ብር ላይ 20ሺህ ብሩን ለሜቄዶንያ አረጋዊያን መርጃ በእርዳታ ሲሰጥ ቀሪውን እያገለገለ ላደገበት ሰንበት ት/ቤት መለገሱን ለአዲስ አድማስ ተናግሯል፡፡
በመዝሙር ሲዲው ውስጥ 11 መዝሙሮች የተካተቱ ሲሆን፤ አምስቱን ለብቻው ሁለቱን ከዘማሪ ዲያቆን ፍቃዱ አዱኛ ጋር በጋራ መስራቱንና ቀሪዎቹ አራት መዝሙሮች በዘማሪ አዱኛ እንደተሰሩ ይገረም ገልጿል፡፡
“የዘመርኩት ማመስገን ስለምወድ” ነው ያለው አርቲስቱ፤ ሌሎችም የተሰጣቸውን ፀጋ ተጠቅመው የድርሻቸውን እንዲያበረክቱ ለማነቃቃት በስራው ላይ መሳተፉን ተናግሯል፡፡  
“ወደፊት ከእኔ ጋር በበጎ ስራዎች ላይ ለመሰማራት የሚፈለግ ሰው ካለ አብሬ ለመስራት ዝግጁ ነኝ” ብሏል - አርቲስት ይገረም ደጀኔ፡፡ አርቲስቱ ከዚህ ቀደም ለአቡነ መልከፀዴቅ ገዳም ለገቢ ማሰባሰቢያ የሚውል የመዝሙር ቪሲዲ ከሙያ አጋሮቹ ጋር መስራቱ ይታወሳል፡፡  

Read 3037 times