የገጣሚ ሶልያና አብዲ “ሼም ይናፍቅሃል” የተሰኘ የግጥም መድበልና ሲዲ ዛሬ ከ3ሰዓት ጀምሮ በጣይቱ ሆቴል ጃዝ አምባ አዳራሽ ይመረቃል፡፡
በመድበሉ ውስጥ የተካተቱት ግጥሞች በሴቶች ጥቃት፣ በህገወጥ ጉዞ አስከፊነት፣ በወጣትነትና በፍቅር ዙሪያ የሚያጠነጥኑ ሲሆን የግጥሙ ሲዲ ደግሞ በኢትዮጵያ ብሔራዊ የእግር ኳስ ቡድኖች (ዋሊያዎቹና ሉሲዎች) ጀግንነት ላይ የሚያተኩር ነው ተብሏል፡፡ 94 ያህል ግጥሞችን የያዘው መድበሉ በ30 ብር ለሽያጭ ቀርቧል፡፡
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና