በደራሲ ብርሃኑ አበጋዝ የተፃፈው “ጥምር ቁስል” ልብወለድ መጽሐፍ ሰሞኑን ገበያ ላይ ዋለ፡፡ መጽሐፉ ትኩረት የደረገው በኢትዮ - ኤርትራ ጦርነትና በሁለቱ ሀገራት ህዝቦች ቁርኝት ላይ ሲሆን የኢትዮጵያና የሶማሊያ ጦርነትም በልብወለዱ ውስጥ ተዳስሷል፡፡ በ161 ገጽ የተቀነበበው ልብወለዱ፤ 37 ክፍሎች ያሉት ሲሆን ታሪኩ በሃሳብ ደረጃ ከተፀነሰ 14 ዓመታት፣ መፃፍ ከተጀመረ ደግሞ ሰባት ዓመታትን እንዳስቆጠረ ደራሲው በመግቢያው ላይ ገልጿል፡፡ ታሪካዊ ልብ ወለድ መጽሐፉ ዛሬ ከቀኑ በ10፡30 በኢዮሃ ሲኒማ የሚመረቅ ሲሆን በ40 ብር ከ60 ሳንቲም እየተሸጠ ይገኛል፡፡
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና