Saturday, 21 June 2014 15:04

በቻናል 3 ከተላለፉ የኢትዮጵያ ፊልሞች ሶስቱ ተሸለሙ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

ካለፈው መጋቢት ወር ጀምሮ “በማቭሪክ ፊልሞች የኢትዮጵያ” አማካኝነት በኢቲቪ ቻናል ሶስት ሲተላለፉ ከነበሩ 12 ፊልሞች ሶስቱ ባለፈው ረቡዕ ምሽት በኢሊሊ ኢንተርናሽናል ሆቴል ተሸለሙ፡፡ ማቭሪክ ፊልሞች የኢትዮጵያ በሚል መጠሪያ በቻናል ሶስት የኢትየጵያ ፎልሞችን ቅዳሜ ምሽት ከ4፡30 ሰዓት ጀምሮ የሚያስተላልፈው ድርጅት ፊልሞቹን ከማስተላለፍ በተጨማሪ በባለሙያዎችና በአዘውታሪ ተመልካቾች የተመረጡና ከ1 እስከ 3 የወጡ ፊልሞችን አወዳድሮ የመሸለም ዓላማ እንደነበረውም የፕሮግራሙ ዳይሬክተር ወ/ሪት ፌቨን ታደሰ በእለቱ ገልፃለች፡፡ ለተከታታይ 12 ሳምንታት ከተላለፉት 12 የአማርኛ ፊልሞች ውስጥ በ2001 ዓ.ም ለእይታ የበቃው “አልተኛም” ፊልም አንደኛ በመውጣት የ20ሺህ ብር ተሸላሚ ሲሆን በ2001 ዓ.ም የተሰራው “የታፈነ ፍቅር” ሁለተኛ በመውጣት የ10 ብር ሽልማት አግኝቷል፡፡ በ2004 ዓ.ም የተሰራው “አየሁሽ” ፊልም ሶስተኛ በመውጣት የአምስት ሺህ ብር ተሸላሚ ሆኗል፡፡
በእለቱ የኢቲቪ የስራ ኃላፊዎች፣ የኪነ-ጥበብ ባለሙያዎች፣ የማቭሪክ ፊልሞች የኢትዮጵያ ስፖንሰር የሆነው ፍሊንት ስቶን ሆምስ ባለቤቶችና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች የተገኙ ሲሆን አርቲስት ስለሺ ደምሴ (ጋሽ አበራ ሞላ) በሙዚቃው ታዳሚዎቹን ሲያዝናና አምሽቷል፡፡

Read 4444 times