በኢትዮ ፊልም ኃ/የተ/የግ/ማህበር አስተባባሪነትና ባለቤትነት የሚዘጋጀው “ጉማ ፊልም ሽልማት” የዘንድሮ ፊልሞችን በሽልማት ውድድሩ ለማካተት ምዝገባ መጀመሩን አስታወቀ፡፡ ለሁለተኛው ዙር የሚወዳደሩ የአምና ፊልሞችን ከመጋቢት 29 እስከ ሚያዚያ 3 በጣይቱ ሆቴል መዝግቦ ማጠናቀቁን የገለፀው ኢትዮ ፊልም፤ በሁለተኛው ዙር ውድድር የዘንድሮዎቹን ለማካተት ከሐምሌ 9 እስከ 16 በጣይቱ ሆቴል ምዝገባ እንደሚያካሂድና ለመመዝገብ ፍላጎት ያላቸው ፊልሞች እንዲመዘገቡ ጥሪ አቅርቧል፡፡ ምዝገባው ከቅዳሜ ከሰዓትና ከእሁድ በስተቀር በስራ ቀናት የሚካሄድ መሆኑንም ድርጅቱ በላከው መግለጫ አስታውቋል፡፡