ባንድነት ተዛምዶ….ያንድነት ተቃርኖ
አንድም በዝማሬ ………አንድም በ’ንጉርጉሮ
አንድም በዝማዌ..አንድም በአንባጓሮ
አንደዜም በብርዱ ……አንደዜም በግለት
አንደዜም በዘፈን…….አንደዜም በማህሌት
እንዲህ እኛ ና ኔ…..አንድም ሆነን ሁለት
ቀናና ጠምዛዛ ………ትጉና ነባዙ
ሐዘንም ይባቤ…….ጥፍጥፍ ጐምዛዛ
እራስና ግርጌ
ግርጌና እራስጌ
አዲስ እና አሮጌ..
በምኞት ትካዜ ከገባን ምናኔ
እኮ እኛ ማነን
ማነኝ እኛ ና’ኔ?!
Saturday, 07 February 2015 13:42
ተጠየቅ
Written by ታደሠ ለገሰ (ሀዋሳ)
Published in
የግጥም ጥግ