Saturday, 07 February 2015 13:42

ተጠየቅ

Written by  ታደሠ ለገሰ (ሀዋሳ)
Rate this item
(3 votes)

ባንድነት ተዛምዶ….ያንድነት ተቃርኖ
አንድም በዝማሬ ………አንድም በ’ንጉርጉሮ
አንድም በዝማዌ..አንድም በአንባጓሮ
አንደዜም በብርዱ ……አንደዜም በግለት
አንደዜም በዘፈን…….አንደዜም በማህሌት
እንዲህ እኛ ና ኔ…..አንድም ሆነን ሁለት
ቀናና ጠምዛዛ ………ትጉና ነባዙ
ሐዘንም ይባቤ…….ጥፍጥፍ ጐምዛዛ
እራስና ግርጌ
ግርጌና እራስጌ
አዲስ እና አሮጌ..
በምኞት ትካዜ ከገባን ምናኔ
እኮ እኛ ማነን
ማነኝ እኛ ና’ኔ?!


Read 3365 times