Saturday, 24 October 2015 08:53

የጠዋት ቡና ሱስ የደም ፍሰትን ያዛባል

Written by 
Rate this item
(2 votes)

    በጠዋት ቡና የመጠጣት ሱስ ያባቸው ሰዎች፤ የለመዱትን ካጡ የደም ፍሰት ሂደታቸውና በአንጎላቸው ውስጥ የሚካሄደው ኤሌክትሪካል ሲስተም እንደሚዛባ አንድ ጥናት አመለከተ፡፡
ሁልጊዜ ጠዋት ጠዋት ቡና የመጠጣት ሱስ ያለባቸው ሰዎች፤ በቡና ውስጥ የሚገኘው ካፌይን በህብለ-ሰረሰራቸው (Spinal cord) ውስጥ የሚገኙትን የደም ቅዳ ቧንቧዎች ያጠባቸዋል፡፡ ይህ መስመር ደሞ ወደ አንጎላችን የሚተላለፍበት ሲሆን የደም ቅዳ ቧንቧዎቹ በመጥበባቸው ምክንያትም ደም ወደ አንጎላችን የሚደርሰው በዝግታ ይሆናል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ካፊይኑ የአንጎልን የኤሌክትሪክ ሲስተም በማዛበት በተጠንቀቅ እንዲቆም ያደርገዋል፡፡ በዚህ ምክንያትም ሰውነታችን ተመጣጣኝ ያልሆኑ ንጥረነገሮችን ይለቃል፡፡ ይህም ወደ አንጎልዎ የሚፈሰውን ደም ይጨምረዋል፡፡ በዚህ ሳቢያም ድንገተኛ የአንጎል ውስጥ ደም መፍሰስ (ስትሮክ) ሊያጋጥምዎ ይችላል፡፡  

Read 6404 times