Saturday, 07 November 2015 09:56

“ሞት በኩላሊት ይብቃ” በጐ አድራጐት ማህበር ሥራ ጀመረ

Written by 
Rate this item
(2 votes)

በሁለት ዓመት 250 ህሙማንን ለማሳከም አቅዷል

 “ሞት በኩላሊት ይብቃ” የተሰኘ በጐ አድራጎት ማህበር፣ ገንዘብ በማሰባሰብ በኩላሊት ህመም የሚሰቃዩና ረዳት የሌላቸውን ህሙማን ለመርዳት ማቀዱን አስታወቀ፡፡
በኩላሊት ህመምተኞች፣ በባለሙያዎችና በበጐ ፈቃደኛ መስራች አባላት የተቋቋመው ማህበሩ፤ሥራ የጀመረ ሲሆን በመጀመሪያዎቹ ሁለት ዓመታት 250 ያህል ህመምተኞችን ለማሳከም እንዳቀደ ተጠቁሟል፡፡
በነገው ዕለት መነሻውን ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል፣መድረሻውን ኢትዮ-ኩባ የወዳጅነት ሀውልት ያደረገ፣ በኩላሊት ህመም መንስኤና መፍትሔ ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ   የእግር ጉዞ እንደሚደረግም ማህበሩ ሰሞኑን በካፒታል ሆቴል በሰጠው መግለጫ አስታውቋል፡፡
የማህበሩ መስራች አቶ ኢዮብ ተወልደ መድህን እንደገለፁት፤የፊታችን አርብ ለኩላሊት ህሙማን መርጃ የገቢ ማሰባሰቢያ ፕሮግራም ይካሄዳል፡፡

Read 4345 times