በተለያዩ ተክሎች ጥቅም ላይ የሚውሉ ፀረ አረም ኬሚካሎች ያለቀናቸው ለሚወለዱ ህፃናት መንስኤ መሆኑን የአለም ጤና ድርጅት አመለከተ፡፡ በአሜሪካ አገር አንድያን ዩኒቨርሲቲ ውስጥ የተደረገውን ጥናት መነሻ በማድረግ ድርጅቱ ሰሞኑን ይፋ ያደረገው ዘገባ እንደሚያመለክተው፤ በናይትሬት የበለፀጉ ፀረ አረም ኬሚካሎችና ማዳበሪያዎች ህፃናት ያለቀናቸው እንዲወለዱና ለተለያዩ የጤና ችግሮች እንዲጋለጡ እያደረጉ ነው፡፡ ነፍሰጡር ሴቶች በተለይም በእርግዝናቸው የመጨረሻ ወራት ለፀረ አረም ኬሚካሎችና ማዳበሪያዎች በስፋት የሚጋለጡ ከሆነ፣ በሆዳቸው በያዙት ፅንስ ላይ ከፍተኛ የጤና ችግር የመፍጠራቸው ዕድል ሰፊ ከመሆኑም በላይ ልጃቸውን ያለቀኑ ለመውለድ ይገደዳሉ ብሏል - ዘገባው፡፡