Tuesday, 29 December 2015 07:29

ከአፍሪካ መሪዎች አንደበት

Written by 
Rate this item
(10 votes)

· ከሥልጣን የሚያወርደኝ የሾመኝ
እግዚአብሔር ብቻ ነው፤ እንግሊዝ ወይም ሌላ
ኃይል አይደለም፤ እግዚአብሔር ብቻ፡፡
ሮበርት ሙጋቤ
· አፍሪካ ከህዝብ ፍላጎት ውጭ ሥልጣን
የሙጥኝ በሚሉ መሪዎች ተሰላችታለች፡፡
ዩዌሪ ሙሴቪኒ
· ዲሞክራሲ የአንድ ጀንበር ክስተት አይደለም፤
ሂደት ነው፡፡
ኃይለማርያም ደሳለኝ
· አንድ ቀን ተመልሰው ይመጣሉ፤ለሽርሽር ነው
የሄዱት፡፡
ኢሳያስ አፈወርቂ
(አገር ጥለው ስለሚሰደዱ ኤርትራውያን
ተጠይቀው የመለሱት)
· ዲሞክራሲ ለአፍሪካ ተብሎ የተፈጠረ
አይደለም፡፡
ሞቡቱ ሴሴሴኮ
(የታንዛኒያ መሪ የነበሩ)
· በመላው ዓለም ከሊቢያ በስተቀር ዲሞክራሲ
ያለበት አገር የለም፡፡
ሙአመር ጋዳፊ
(የቀድሞው የሊቢያ መሪ)
· የግብጽ ህዝብ ከሥልጣን እንድወርድ ከፈለገ፣
ደህና የአገልግሎት ካሳ ሊሰጠኝ ይገባል፡፡
ሆስኒ ሙባረክ
(የቀድሞው የግብጽ ፕሬዚዳንት)

Read 4080 times