Saturday, 11 February 2017 12:54

የዘላለም ጥግ

Written by 
Rate this item
(6 votes)

(ታላላቅ ሰዎች
በመሞቻቸው ሰዓት)
- “ማምለጫ ሰበብ እየፈለግሁ ነው”
ደብሊው ሲ. ፊልድስ
(አሜሪካዊ የፊልም ተዋናይና ኮሜዲያን)
- “በእግዚአብሔር እ መኑ እ ናም ም ንም
የሚያስፈራችሁ ነገር አይኖርም”
ጆናታን ኤድዋርድስ
(የክርስቲያን ሰባኪና የስነ-መለኮት ልሂቅ)
- “ምድር ወደ ኋላ ስትሸሽ፣ መንግስተ ሰማያት
ሲከፈት ይታየኛል፡፡ እግዚአብሔር እየጠራኝ
ነው”
ዲ.ኤል.ሙዲ
(አሜሪካዊ ወንጌላዊና ደራሲ)
- “ሞት፤ የዘላለማዊነትን ቤተ መንግስት
የሚከፍት ታላቅ ቁልፍ ነው”
ጆን ሚልተን
(የብሪቲሽ ገጣሚ)
- “በአስር ደቂቃ ዘግይቻለሁ፡፡ እኔ ማርፈድ
አልወድም፡፡ ፀሎቱ ጋ ልክ በ11 ሰዓት መገኘት
እፈልጋለሁ፡፡”
ማሃትማ ጋንዲ
(የህንድ የነፃነት ንቅናቄ መሪ)
- “ዛሬ በጣም ሞቃት ነው”
ጄሲ ጄምስ
(አሜሪካዊ የባቡር ላይ ዘራፊ)
- “ሁልጊዜም ጋደም ስል የተሻለ እናገራለሁ”
ጄምስ ማዲሰን
(የአሜሪካ 4ኛ ፕሬዚዳንት)
- “በቃ ተይኝ!”
(ነርሷ የእግር እንቅስቃሴ እንዲያደርግ ስትጠይቀው)
ጎሬ ቪዳል
(አሜሪካዊ ደራሲ)
- “እስቲ ወደ አባታችን ቤት ልሂድ”
ጆን ፖል (ዳግማዊ)
(የሮማን ካቶሊክ ቤ/ክርስቲያን ጳጳስ)
- “ለብቻዬ ተይኝ፤ ደህና ነኝ”
(ለነርሱ የተናገረው)
ባሪ ዋይት
(አሜሪካዊ ሙዚቀኛ)
- “እና ሞት ይሄ ነው - ይሁና”
ቶማስ ካርሊሌ
(የስኮትላንድ ፈላስፋና የታሪክ ምሁር)
- “የሰሙኝ እንኳን አይመስለኝም”
(ራሱን ከማጥፋቱ በፊት የተናገረው)
ዩክዮ ሚሺማ
(ጃፓናዊ ደራሲ)

Read 5369 times