Error
  • JUser: :_load: Unable to load user with ID: 62
Print this page
Saturday, 12 May 2012 08:54

አሜሪካዊው ታጋች፤ ነፍሱን እንዲታገደጉት ጠየቀ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

ባለፈው አመት ፓኪስታን ውስጥ በአልቃይዳ የታገተው አሜሪካዊ፤ ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ ከአጋቾቹ ጋር ተገናኝተው ህይወቱን እንዲታደጉ ጠየቀ፡፡ በአጋች ቡድኑ የተሠራጩ የቪዲዮ እና የኢንተርኔት መረጃዎች እንዳመለከቱት ታጋቹ ዋረን ዋይንስተን ኦባማ ከአጋቾቹ የቀረበላቸውን ጥያቄ በመቀበል ህይወቱን ከሞት እንዲያተርፉለት ተማጽኗል፡፡ “ክቡር ፕሬዚዳንት፤ ህይወቴ በእርስዎ እጅ ናት ጥያቄያቸውን ከተቀበሉ እኔ በህይወት እኖራለሁ፡፡ ጥያቄያቸውን ካልተቀበሉ እሞታለሁ” ብሏል - በመልዕክቱ፡፡

ታጋቹ ለባለቤቱ ባስተላለፈው መልዕክትም፤ ባለቤቱዋ በደህና ሁኔታ  ላይ እንዳለ እንድታውቅና የሚያስፈልጉትን ህክምናዎች በሙሉ እንደሚያገኝ እንድታውቅ እንደሚፈልግ ገልጿል፡፡

የአልቃይዳው መሪ አይመን አልዛዋሪ፤ ባለፈው ታህሳስ ወር ለዋረን ዋይንስተን መታገት አልቃይዳ ሀላፊነቱን እንደሚወስድ በመግለፅ፤ አሜሪካ የታሊባን እስረኞችን እንድትለቅ፣ በፓኪስታን በአፍጋኒስታን፣ የመን፣ ሶማሊያ እና ጋዛ የምታደርገውን የአየር ድብደባም እንድታቆም ጠይቆ ነበር፡፡

የዋይት ሀውስ ቃል አቀባይ ጄይ ካርኔ በጉዳዩ ላይ በሰጡት መግለጫ፤  ዋረን በአስቸኳይ እንዲለቀቅ ጠይቆ “ከአልቃይዳ ጋር መደራደር አንችልም፤ አንደራደርምም” ብለዋል፡፡

 

 

Read 3105 times Last modified on Saturday, 12 May 2012 08:58

Latest from