Print this page
Saturday, 26 October 2019 11:50

‹‹ወይ አያ እገሌ፤ ጉድ አደረገኝ ትርፉን ነግሮ መከራውን ሳይነግረኝ!!››

Written by 
Rate this item
(6 votes)

ከዕለታት አንድ ቀን የቆላና የደጋ ገበሬዎች ነበሩ፡፡ ሁለቱም በችግርና በጉስቁልና ሲኖሩ ሳለ፣ አንድ ቀን አንደኛው፣ ሳር ቤቱን ትቶ፣ ቆርቆሮ ቤት ቀየረ፡፡ አጥሩም በአዲስ መልክ ታጠረ፡፡
የጥንት ግጥም የሚቀጥለውን ይላል፡-
አልኩሃ ምን ትሆን?
እኔም እናትህ ነኝ አንተም ልጄ ብትሆን
ይቺን ጨቅላ መጽሐፍ የምታነብ ሁሉ
አደራ ስለ እኔ ማሪያም ማሪያም በሉ
ከሃያ ስድስቱ ወንዶች ፊደላት
አርግዣለሁና መዝገበ ቃላት
ስንት እልፍ አበው ናቸው አርግዘው የሞቱ
ቀኝ እጃቸው አጥሮ ፊደል በማጣቱ
ለትምህርት አይደለም ይህን መናገሬ
ለማስቀናት እንጂ ሰነፉን ገበሬ
ሃዋርያው ሲናገር ወደ ምዕመናኑ
ለምትበልጥ ፀጋ ይላል ቅኑ አስቀኑ
        * * *
ዛሬ ርዕሰ አንቀፁን በግጥም ያቀረብነው፣ ትንሽ ወዝ እናክልበት ብለን ነው!
ሁላችንም በጋራ ከተንቀሳቀስን የጋራ ግብ ይኖረናል!
ፊት ለፊት እንሂድ!
እንቅፋት አንፍራ!
ትላንትናን አበክረን እንይ!
‹‹ነገም ሌላ ቀን ነውን›› አንዘንጋ!
ያመለጡን ዕድሎች አያሌ ናቸውና ሀሳቡን ብቻ እናብሰልስለው፡፡
ሁኔታዎችን እያጤንን መንገዳችንን ልብ እንበል፡፡   
ብዙ መጓዛችንን እናስተውል፡፡
ገና ብዙ እንደምንጓዝ አይጥፋን፡፡
ዞሮ ዞሮ መንገዱ ረዥም ነው!
ለዳገት የጫነው፣ ሜዳ ላይ እንዳይደክም ጉልበታችንን እናክም!
ወዴት እንደምንሄድ በትክክል እንወቅ!
ደጋግመን ያልነውን ዛሬም እንበለው፡-
እኔ መች ፈልጌ ሕይወት ያለችግር
መንፈሴስ መች ሽትቷ ራሷ ግር
ለታላቁ አላማ አለው መልካም ዕድል
ሕይወቴ ትሞላ ትሁን የትግል ድል!
… የሁላችን ሂደት የሁላችን ዕድል
የሚል ነው አንድ አካል
አይበቃም ያሉት ሰው ተርፎ እንዴት ይገኛል?
ከሚለው አያልፍም ሁሉም ገፁ አንድ ነው
ዓለም እንደዚህ ነው
አገር እንደዚህ ነው
ሰፈር እንደዚህ ነው
ሕይወት ይህ ብቻ ነው!
በአዲሱ  ዘመን፤ በጎ በጎው ሁሉ ለአገራችንና ለህዝቦቿ!!

Read 11661 times
Administrator

Latest from Administrator