Print this page
Saturday, 02 November 2019 12:39

‹‹አሥራ ስድስቱን ዝንጀሮዎች ባንድ ጥይት ሰፋኋቸው›› ቢለው፤ ‹‹እኔን የገረመኝ ያንተ አገር ዝንጀሮዎች አሰላለፍ ነው!›› አለው

Written by 
Rate this item
(3 votes)

 ‹‹ታመመ ቢሏቸው አንበሳ ባለበት
ሊጠይቁት ሄዱ የምድር ሁሉ አራዊት
ይሄንኑ ሰምታ የጦጣ ብልጣ - ብልጥ
ሳትጠይቀው ቀረች ሳትገባ ወደ ውስጥ
ለምን ብለው ቢሏት መለሰች ጦጢቷ
የገቡት ሳይወጡ ጉዱ ሳይጣራ ቀኑም ሆነ ሌቱ
እንዴት ብዬ እጄን ልስጥ እስከ ማዕሌቱ
አራዊቱ ለአንበሳ ያላቸው ክብር እጅግ ድንቅ ነው፡፡ ሲታመም እጅግ አሳሰባቸው እንጂ ይሄ ጉልበተኛ በቃ እጁን ይሰጠናል ብለው አሰቡ፡፡ አያ አንበሶ ግን ይብሱን ጉልበት አፈራና ፈረጠመ፡፡ አራዊቱም በጣም ፈሩት፡፡
ከዚያም በሁለት ተከፈሉ፡፡
አንደኞቹ፡-
‹‹ምነው እንዳመመው በዛው በቀሩ››
ከፊሎቹ፡-
‹‹አይ የሚፈራ መሪ ወሳኝ ስለሆነ አያ አንበሶ ያስፈልገናል›› አሉ፡፡
በዚህ አጠቃላይ ግንዛቤ ከብዙ ክርክር በኋላ ተግባቡ፡፡ አያ አንበሶም ሙሉ ለሙሉ አገገመና የዱር አራዊቱን እየተጎማለለ መጎብኘት ጀመረ!
‹‹ታምሜ በመንከባከባችሁ አመሰግናለሁ ትልቅ ውለታ ጥላችሁብኛል!›› አላቸው፡፡
***
አገራችን አንድ መንገድ አጥታለች ወይም ጠፍቶባታል፡፡ ብዙ ሆነን አንድ አገር ማቅናት ዳገት ሆኖብናል፡፡ ማሻሻል አቅቶናል። ለችግሮቿ መፍትሄ አጥተናል፡፡ መንገድም ጠፍቶብናል፡፡
‹‹እንግዲህ ለፍቅር መንገድ አልሰጠውም
ሲገኝ እየጠጣሁ እተኛለሁ የትም›› ማለት ይቀላል፡፡
‹‹ያለፈ ጥረታችንን ሳስታምመው ትዝ ሲለኝ
ከሞከርነው ነገር ይልቅ ያልሞከርነው ነው እሚቆጨኝ›› ማለትም ከሀምሌት ጋር ያዋጣናል፡፡
የሚሰማንን እንጻፍ፡፡ የምንጽፈውም ይሰማልን! በተቻለን ስሜቶቻችንን እንታዘዛቸው፡፡
ዕውነትን ፍለጋ በቆፈርነው ምድር
እህል ዘራንበት በልተን እንድናድር
እንነሳ!
እናብር!
እንተባበር!
እናልም!
እንመንብ!
ክፍተት አንተው!
እንንቀሳቀስ!
እንላወስ!!

Read 11437 times
Administrator

Latest from Administrator