Saturday, 04 July 2020 00:00

የግጥም ጥግ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)


 የማይነጋ ምሽት
በዚህ ሃገር ሰማይ
ጨረቃ የለችም
ወይም ተሰዳለች
አሊያም ከናካቴው አልተፈጠረችም።
በዚህ ሃገር ሰማይ
ከዋክብትም የሉም
በብርሃናቸው፤ ሰማይ አያስጌጡም፡፡
ሰማዩም መልክ የለው
ያገሬን አይመስል
ፀሃይ ትበርዳለች
በግዜ ይመሻል።
በዚህ ሃገር ሰማይ
ወፎችም አይበሩም
በጥዑም ድምፃቸው
ንጋት አያበስሩም።
(ለውብ የሃገሬ ምሽት፤ ከባህር ማዶ)

Read 2146 times