የቀድሞው የአለማችን የእግር ኳስ ኮከብ አርጀንቲናዊው ዲያጎ አረማንዶ ማራዶና፣ ባለፈው ሳምንት የተሳካ የአንጎል ቀዶ ህክምና እንደተደረገለት መነገሩን ቢቢሲ ዘግቧል፡፡
በደም ማነስ ሲሰቃይ የቆየው የ60 አመቱ ማራዶና ባለፈው ሰኞ ቦነስ አይረስ ውስጥ ወደሚገኝ አንድ ክሊኒክ መወሰዱን ያስታወሰው ዘገባው፤ በአንጎሉ ውስጥ የደም መርጋት ችግር በመገኘቱ 80 ደቂቃ የፈጀ የተሳካ ቀዶ ህክምና እንደተደረገለት የግል ሃኪሙ መናገራቸውን አመልክቷል፡፡
ማራዶና ከቀዶ ህክምናው በኋላ በጥሩ ጤንነት ላይ እንደሚገኝና እንዳገገመ የጠቆመው ዘገባው፤ በርካታ አድናቂዎቹና ደጋፊዎቹ ከሆስፒታል ሲወጣ ጠብቀው ስሙን እየጠሩ ደስታቸውን እንደገለጹለትም አስረድቷል፡፡