Print this page
Saturday, 07 November 2020 13:54

ማራዶና የተሳካ የአንጎል ቀዶ ህክምና ተደረገለት

Written by 
Rate this item
(0 votes)

  የቀድሞው የአለማችን የእግር ኳስ ኮከብ አርጀንቲናዊው ዲያጎ አረማንዶ ማራዶና፣ ባለፈው ሳምንት የተሳካ የአንጎል ቀዶ ህክምና እንደተደረገለት መነገሩን ቢቢሲ ዘግቧል፡፡
በደም ማነስ ሲሰቃይ የቆየው የ60 አመቱ ማራዶና ባለፈው ሰኞ ቦነስ አይረስ ውስጥ ወደሚገኝ አንድ ክሊኒክ መወሰዱን ያስታወሰው ዘገባው፤ በአንጎሉ ውስጥ የደም መርጋት ችግር በመገኘቱ 80 ደቂቃ የፈጀ የተሳካ ቀዶ ህክምና እንደተደረገለት የግል ሃኪሙ መናገራቸውን አመልክቷል፡፡
ማራዶና ከቀዶ ህክምናው በኋላ በጥሩ ጤንነት ላይ እንደሚገኝና እንዳገገመ የጠቆመው ዘገባው፤ በርካታ አድናቂዎቹና ደጋፊዎቹ ከሆስፒታል ሲወጣ ጠብቀው ስሙን እየጠሩ ደስታቸውን እንደገለጹለትም አስረድቷል፡፡

Read 999 times
Administrator

Latest from Administrator