Thursday, 14 January 2021 11:41

የወግ ጥግ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

 ንግሥት ዘውዲቱ ደብረ ብርሃን በአንድ ገዳም አንድ  ካህን ሾሙ። ያ ካህን ባሪያ ኖሯል። ስለዚህም ካህናቱ አልወደዱትም። በዚያ ላይ የተለመደውን የካህናቱን ግብር ሳያበላ ቀረና ንግስት ዘንድ ከሰሱት- ካህናቱ ተቆጥተው ማለት ነው። ችሎት ቀረቡ ተካሰው።
ንግሥትም- “አንተ፣ ምን ሆነህ ነው የተለመደ ግብራቸውን ሳታበላቸው የቀረኸው?” አሉና ጠየቁት።
ካህኑም- “ንግሥት ሆይ፤ እኔ ለስንት ጅብ ላበላ ነው?!!" አለና መለሰ
ይሄኔ- ከካህናቱ አንዱ፡-
“እንግዲያውስ ንግሥት ሆይ፤ ይህ ካህን ይነሳልን። ለነገሩ አንድ አህያስ ለስንት ጅቦች ሊሆነን ነው? ይነሳልን!”
ማስታወሻ፡- አህያ ነው ያሉት ባሪያ ነው ለማለትም ነው፤ በዚያ ዘመን ቋንቋ፡፡


Read 1431 times