Saturday, 16 January 2021 12:08

የግጥም ጥግ

Written by 
Rate this item
(13 votes)

ያንቺን ድምፅ ብቻ፣ ሲያቃጭል የኖረ
የቆለፍሺው ጆሮ፣ በምን ተሰበረ?
ይኸው ብዙ ድምፆች
ከየትም እየመጡ፣ ይሰሙኝ ጀመረ።
የዘጋሽው ልቤ!
የቆለፍሽው ልቤ!
የተሰባበረው
እንዴት ሰው አማረው?
። ። ።
ልረሣሽ ነው መሠል፣ ወይ ደግሞ
ልትመጪ
ይሰማኝ ጀመረ
ያውደኝ ጀመረ
ይታየኝ ጀመረ፣ ሕይወት ካንቺ ውጪ።
(በላይ በቀለ ወያ)


__________________


          የዕድሜ ልክ ደብዳቤ

ይድረስ ለምወድሽ…
ዓለም ያክል ሐሳብ የተሸከመ ሰው፣
ዕረፍት አያገኝም ፍቅር ቢዳብሰው።
ቢሆንም እውነታው፣
ሞቴ አንች ነሽና…!


Read 2944 times