Tuesday, 26 January 2021 00:00

ሳዑዲ አረቢያ በ500 ቢሊዮን ዶላር የበረሃ ከተማ ልትቆረቁር ነው

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

   የሳዑዲ አረቢያው ልዑል መሃመድ ቢን ሰልማን በአገሪቱ ሰሜን ምዕራብ አካባቢ በሚገኘው ኒኦም በረሃ ውስጥ 500 ቢሊዮን ዶላር ወጪ የሚደረግበት ልዩ ከተማ ሊቆረቁሩ መሆኑን ገልፍ ኒውስ ዘግቧል፡፡
የሃይል አቅርቦቱን ከንጹህ ታዳሽ ሃይል ምንጮች እንደሚያገኝ የተነገረለትና “ዘ ላይን” የሚል ስያሜ የተሰጠው ይህ ዘመናዊ ከተማ፣ አንድ ሚሊዮን ያህል ህዝብ እንዲኖርበት መታቀዱንም ዘገባው አመልክቷል፡፡
አዲሱ የበረሃ ከተማ ምንም አይነት በነዳጅ የሚሰሩ መኪኖች እንደማይገቡበት የተነገረ ሲሆን፣ አገሪቱ ኒኦም የተሰኘውን በረሃ ከፍተኛ የቱሪዝም እና የቢዝነስ ማዕከል ልታደርገው ያሰበችው በቀይ ባሕር ዳርቻ ላይ የሚገኝ ስፍራ መሆኑን የጠቆመው ዘገባው፣ አገሪቱ እ.ኤ.አ በ2030 ከነዳጅ ጥገኝነት ለመላቀቅ ለያዘችው ዕቅድ መሳካት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረክታል ተብሎ እንደሚጠበቅም አክሎ ገልጧል፡፡

Read 2886 times