Saturday, 06 February 2021 14:32

የግጥም ጥግ

Written by 
Rate this item
(9 votes)

   ናፍቆት

ሰማዩ ቀልጦ







ብርሀን አፍሮ ይሽኮረመማል፣
ጨለማ ሆኗል፤
ውኃ ተገርፎ እሳት ያነባል፣
የምድር ገላ ይገሸለጣል፤
ጽልመት ጎምርቶ፣
ፍሬ ያፈራል የመርገምት እጽ ያጎነቁላል፤
አንቺ ሳትኖሪ፣
ይህን ይመስላል፡፡
(ሳሙኤል በለጠ-ባማ)

Read 2935 times
More in this category: « ሰውነት ዛጎል »