ቻይና በአለማችን በግዙፍነቱ ወደር አይገኝለትም የተባለውን እጅግ ግዙፍ የኤሌክትሪክ ሃይል ማመንጫ ግድብ በቲቤት ግዛት ከሂማሊያ ተራሮች ግርጌ በሚገኘው የርሉንግ ሳንፖ ወንዝ ላይ ልትገነባ ማቀዷን አልጀዚራ አስነብቧል፡፡
60 ጊጋ ዋት የኤሌክትሪክ ሃይል የማመንጨት አቅም እንደሚኖረው የተነገረለት ይህ ግዙፍ ግድብ፣ በአለማችን ትልቁ ግድብ የሆነውና ስሪ ጎርጅስ የተሰኘው የቻይና ታዋቂ ግድብ ከሚያመነጨው ሃይል በሶስት እጥፍ የሚበልጥ ሃይል እንደሚያመነጭም ዘገባው አመልክቷል፡፡
ቻይና እ.ኤ.አ እስከ 2060 ከካርቦን ነጻ ኢኮኖሚ ለመገንባት የያዘችው ዕቅድ አካል እንደሆነ ከተነገረለት ከዚህ ግዙፍ ግድብ ግንባታ ጋር በተያያዘ ከ14 ሺህ በላይ ሰዎች ከመኖሪያ አካባቢያቸው ይፈናቀላሉ መባሉንና ይህም ከቲቤታውያን ዘንድ ተቃውሞ እንደገጠመው ዘገባው ገልጧል፡፡
Published in
ከአለም ዙሪያ