Print this page
Saturday, 20 March 2021 11:54

ኤምአይቲ የአመቱ የአለማችን ምርጥ ዩኒቨርሲቲ ተባለ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 የአመቱ የአለማችን ምርጥ ዩኒቨርሲቲዎች ዝርዝር ከሰሞኑ ይፋ የተደረገ ሲሆን፣ ላለፉት 9 ተከታታይ አመታት በአንደኛነት የዘለቀው የአሜሪካው ማሳቹሴትስ ኢንስቲቲዩት ኦፍ ቴክኖሎጂ (ኤምአይቲ) ዘንድሮም ክብሩን ማስጠበቁ ተነግሯል፡፡
የትምህርት አሰጣጥ ጥራት፣ የምርምርና ልቀት ማዕከልነት አቅምን ጨምሮ በ6 መስፈርቶች ተጠቅሞ የአለማችንን ዩኒቨርሲቲዎች በመገምገም የተሰራው የአመቱ ሪፖርት፣ በሁለተኛነት ደረጃ ላይ ያስቀመጠው ስታንፎርድ ዩኒቨርሲቲን ሲሆን፣ ሃርቫርድ በ3ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል፡፡
የአሜሪካው ካሊፎርኒያ ኢንስቲቲዩት ኦፍ ቴክኖሎጂ፣ የብሪታኒያው ኦክስፎርድ፣ የስዊዘርላንዱ ስዊዝ ፌዴራል ኢንስቲቲዩት ኦፍ ቶክኖሎጂ፣ የብሪታኒያው ካምብሪጅ፣ የብሪታኒያው ኢምፔሪያል ኮሌጅ ለንደን፣ የአሜሪካው ዩኒቨርሲቲ ኦፍ ቺካጎ እና የብሪታኒያው ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ ለንደን በዘንድሮው የአለማችን ምርጥ ዩኒቨርሲቲዎች ዝርዝር ውስጥ እንደ ቅደም ተከተላቸው ከአራተኛ እስከ አስረኛ ያለውን ደረጃ የያዙ ዩኒቨርሲቲዎች መሆናቸውን ሪፖርቱ ያሳያል፡፡
በአለም ዙሪያ በሚገኙ 5 ሺህ 500 ዩኒቨርሲቲዎች ላይ ጥናት በማድረግ የአመቱን 1 ሺህ 29 ምርጥ ዩኒቨርሲቲዎች ዝርዝር ይፋ ያደረገው ኪውኤስ የተባለው ተቋም፤ ከአፍሪካ ካካተታቸው ዩኒቨርሲቲዎች መካከል 220ኛ ደረጃን የያዘው የደቡብ አፍሪካው ዩኒቨርሲቲ ኦፍ ኬፕታውን፣ 403ኛ ደረጃን የያዘው ሌላኛው የአገሪቱ ተቋም ዩኒቨርሲቲ አፍ ዊትዋተርስራንድ እና 411ኛ ደረጃ ላይ የተቀመጠው የግብጹ አሜሪካን ዩኒቨርሲቲ ኦፍ ካይሮ ይገኙበታል።

Read 2050 times
Administrator

Latest from Administrator