(መጥበብ፤ መስፋት እና መንቃት) የትረካ መጽሀፍ በገበያ ላይ ዋለ
በኤደን ሀብታሙ የተፃፈው ለደራሲዋ የበኩር ስራዋ የሆነው “ከአመጿ ጀርባ” የተሰኘ መፅሀፍ በገበያ ላይ ዋለ፡፡
ደራሲዋ ከታሪክ አወቃቀር እስከ ትረካ ስልት፣ የገፅ-ባህሪይ አሳሳልና አሰያየም ድረስ ገፀ- ባህሪያቱ ከአንባቢያን ጋር ለመሰማማትና ለመስማማት እንዲችሉ አድርጋ አቅርባዋለች።
መፅሀፍ ስለ ፍቅር፣ ስለ ማህበራዊ ኑሮ እና የተለመደውን የለተለት የኑሮ ዘይቤ ለማሸነፍ የሚደረገውን ግብግብ በልዩ አቀራረብና በማራኪ ገፅታ ተርካልናለች፡፡
መፅሀፉ በሰባት ክፍሎች እና በ214 ገፆች የተቀነበበ ሲሆን በ150 ብር እና በ10 ዶላር ለገበያ ቀርቧል፡፡