Saturday, 10 April 2021 12:03

የኮሪያ ዘማቾች ማህበር ፕሬዝዳንት አረፉ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

   የቀብር ስነ ስርአታቸው ዛሬ ይፈፀማል

               የኮሪያ ዘማቾች ማህበርን ላለፉት 10 ዓመታት በፕሬዝዳንትነት ሲያገለግሉ የቆዩትና በቃኘው ሻለቃ ጦር ወደ ኮሪያ በመዝመት አርበኛ ወታደር ኮሎኔን መለሰ ተሰማ ከዚህም ዓለም በሞት ተለዩ፡፡
ማህበሩ በትናትናው ዕለት በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ እንደተናገረው ኮሎኔል መለሰ አገራቸው ወደ ኮሪያ ባዘመታቸው ወቅት ከሌሎች ጓዶቻቸው ጋር በመሆን ታሪክ የማይዘነጋው ታላቅ ድል አስመዝግበዋል፡፡ ኮሎኔል መለሰ የኮሪያ ዘማቾች ማህበርን በማጠናከር፣የማህበሩን ህንጻና መዝናኛ ፓርክ ባመረ ሁኔታ እንዲሰራ ከፍተኛ ጥረት ያደርጉና ለኮሪያ ዘማች ልጆችና የልጅ ልጆች በስኮላር ሽፕ የትምህርት ዕድልና ሌሎች ጥቅማ ጥቅሞች እንዲያገኙ በማድረጉ ረገድ ከፍተኛ ሲያደርጉ መቆየታቸው ተናግሯል፡፡
ኮሎኔል መለሰ በደረሰባቸው ህመም ምክንያት መጋቢት 30 ቀን 2013 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት የተለዩ ሲሆን የቀብራቸው ስነ-ስርዓትም በዛሬው ዕለት በቅድስት ስላሴ ካቴድራል እንዲፈፀም ተገልጿል፡፡

Read 980 times