የአለማችን አጠቃላይ ወታደራዊ ወጪ ባለፈው በፈረንጆች አመት 2020 ወደ 2 ትሪሊዮን ዶላር ከፍ ማለቱንና ከሰሞኑ የወጣ አንድ ሪፖርት አስታውቋል፡፡
ስቶክሆልም ኢንተርናሽናል ፒስ ኢንስቲቲዩት የተባለው ተቋም ከሰሞኑ ባወጣው አለማቀፍ ሪፖርት እንዳለው፣ በአመቱ ከፍተኛውን ወታደራዊ ወጪ ያደረገቺው ቀዳሚዋ የአለማችን አገር አሜሪካ ስትሆን 778 ቢሊዮን ዶላር ያህል ወጪ አድርጋለች፡፡
ላለፉት 26 ተከታታይ አመታት ወታደራዊ ወጪዋ ማደጉን የቀጠለው ቻይና፤ በ252 ቢሊዮን ዶላር ሁለተኛ ደረጃ ላይ ስትገኝ፣ ህንድ በ72.9 ቢሊዮን ዶላር ሶስተኛ፣ ሩስያ በ61.7 ቢሊዮን ዶላር አራተኛ፣ ብሪታኒያ በ59.2 ቢሊዮን ዶላር አምስተኛ ደረጃን መያዛቸውንም ሪፖርቱ ይጠቁማል፡፡
በአመቱ ከተመዘገበው አጠቃላይ አለማቀፍ ወታደራዊ ወጪ ውስጥ 2 በመቶ ያህሉን ያወጡት አሜሪካ፣ ቻይና፣ ህንድ፣ ሩስያና ብሪታኒያ መሆናቸውንም አመልክቷል፡፡
Published in
ከአለም ዙሪያ