በሰምና ወርቅ ሚዲያና ኢንተርቴይመንት በየወሩ የሚካሄደው የኪነ-ጥበብ ምሽት የዚህ ወር መሰናዶ “ያንተም ቤት ሲንኳኳ” በሚል ርዕስ የፊታችን ማክሰኞ ግንቦት 10 ቀን 2013 ዓ.ም ከቀኑ 11፡00 ጀምሮ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር ይካሄዳል።
በዕለቱም ዲስኩር፣ ወግና ግጥም የሚቀርብ ሲሆን ዳኛቸው አሰፋ (ዶ/ር)፣ ወዳጄነህ መሃረነ፣ ደራሲና ጋዜጠኛ ጥበቡ በለጠ፣ ጋዜጠኛ ወንድሙ ሀይሉ፣ መስረም ላቺሳ (ዶ/ር) እንዲሁም ገጣሚያኑ በቃሉ ሙሉ፣ ማርታ ዳዲ፣ ህሊና ሀዋዝ፣ ዳግም ደጀኔና ቶፊቅ መሃመድ ስራዎቻቸውን ያቀርባሉ ተብሏል። የመግቢያ ዋጋ 100 ብር ሲሆን ትኬቶቹ በጃፋር ፣ በዮናስ፣ በዘውዱ፣ በእውቀት በርና በጦቢያ መፃህፍት መደብሮች ይገኛሉ።