“ሰው ለሰው” እና “ዘመን” በተሰኙት ተከታታይ የቴሌቪዥን ድራማዎቹ፣ “ዙምራ” በተሰኘው ፊልሙና በሬዲዮና በመድረክ ድራማ ድርሰቶቹ ዕውቅናን ያተረፈውና በቅርቡ በኮሮና ቫይረስ ህይወቱን ያጣው አርቲስት መስፍን ጌታቸው ባለፈው ሀሙስ ከቀኑ 7፡00 ጀምሮ በብሔራዊ ቴአትር ተዘከረ።
በሥነ-ስርዓቱ ላይ ስራዎቹን የሚገልፅ አጭር ዘጋቢ ፊልም፣ የህይወት ታሪኩ በፅሁፍ ከ”ሰው ለሰው” ተከታታይ ድራማው ላይ የተቀነጨበ ተውኔት በተዋንያኑና ሌሎችም ጥበባዊ ስራዎች የቀረቡ ሲሆን መስፍን ለሀገር ኪነ-ጥበብ ለዋለው ውለታና ታታሪነቱ ምስጋና ቀርቦለታል።
በዚህ የአርቲስቱ የዝክር መርሃ ግብር ላይ ቤተሰቦቹ፣ የስራ ባልደረቦቹ፣ ወዳጅ ዘመዶቹ፣ የመንግስት ስራ ሃላፊዎችና የኪነ-ጥበብ አድናቂዎች የታደሙ ሲሆን ለከያኒው ያላቸውን አክብሮትና ፍቅር ገልፀዋል።
Saturday, 22 May 2021 12:48
አርቲስት መስፍን ጌታቸው በኪነ-ጥበብ ስራዎቹ ተዘከረ
Written by ናፍቆት ዩሴፍ
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና